Get Mystery Box with random crypto!

+++ይህን ገዳም ተዓምር አንብቡ!ሰሜን ሸዋ መንዝናይፉት መዘዞ[አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ] መ | አቡነ እጨጌ ዮሐንስ ዘጠገሮ ገዳም ፨ Johnny aleme

+++ይህን ገዳም ተዓምር አንብቡ!ሰሜን ሸዋ መንዝናይፉት መዘዞ[አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ] መስቀሉ የሚያለቅስበት እና ከለሩ የሚቀያየርበት/ አፋሮ አይገባ /መስቀል ያለበት።

ወዳጆች በተለይ ውጭና መሄድ የማትችሉ ተሳሉ እርሱ አያሳፍርም እውነት አምነን መንገር መሳል ብቻ በየአላችሁበት ችግራችሁን አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ይፍታላችሁ!
ጤናችሁን ይስጧችሁ!
በሽታውን ያጥፉልን!አሜን!!!

SHARE!ያደረገውን ያሳወቀውን ገዳሙን አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ያሰበውን ይፈጽምለት።
አንብቡት በረከት ነው ንገሩት የውስጣችሁን ተሳሉ አታፍሩም ወድያው ምላሽ እናገኛለን፤በየአላችሁበት ይስማችሁ!አሜን!!!shareበውጭ ያላችሁ መሳል መንገር ብቻ ይህ" አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ" ገዳም ቀደምት እና ጥንት በመላዕክት የመጣ በኢትዮጵያ በአለም ትልቁ ታቦት ነው።
በጣም ስለት ስለሚሰማ የምትረሱ አትሳሉ ምክንያቱም ስለት በዕለት የነገሩትን ስለሚመልስ ነው ከረሳችሁ ቁጡ ነው አደጋ አለው።
በዚህ ገዳም ይህ የምታዩት /ዛፍ ጸበሉ/ ነው ከዚህ ዛፍ ውስጥ የሚወጣው ጸበል ቀይ ሲሆን ጸበሉም ቃልኪዳን ያለው "ለአይንና ለጆሮ ህመም "ብቻ ነው፤በዚህ ጸበል የማያየው አይነ ስውራን አይናቸው የበራው እረ ብዙ ነው ለቁጥርም ያዳግታል።ጆሮ የማይሰማው እረ ስንቱ ሰምቷል።ሌላም የምንጠመቀው ከገደል ውስጥ የሚፈልቅ ጸበል ስንቱ በሽተኛ ነው የዳነው በተለይ የአናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ "እምነቱን የተቀደሰበት"የታመመን በዕለት የሚፈውስ እምነት ነው።በእምነቱ እኔም ምስክር ነኛ የሄደ ሁሉ የሚመሰክርበት ገዳም ነው የስለቱ ነገር አይነሳ።
ጾም ባልሆነ ወቅት ስለት የተሳሉ ሰዎች ለምሳሌ በግ ከሆነ በጉን ወስደው ቤተክርስትያን ውስጥ ሲያርዱ ለክብረ በዓል የመጣው ሰው ሁሉ ቢላ ጩቤ ይዞ ነው የሚመጣው ምክንያቱም ያ የስለት በግ የተሳለው ስውየ በጉን እንዳረደው አንገቱን እንዳረደ በገዳሙ ውስጥ ለክብረ በዓል የመጣው ሰው ሁሉ ይከበዋል አንገቱ እንዳረደ ሌላውን ህዝብ በሽሚያ ነው የሚናጠቀው ግማሹ እግሩ ሌላ የተለያዩ የስጋውን አካል በሽሚያ ቢላ ጩቤ የያዘ ሁሉ እየገነጣጠሉ የሚሻሙበት ገዳም ነው ምክንያቱም የስለት በግ ስጋው በጣም ብዙ የታመሙን አልጋ ላይ ያሉ በመንፈስ የሚሰቃዩን ስለሚፈውስ ነው።ስለት የማይገባ የለም ያለውን ሰዉ ያለዉን ይሰጣል ድመት ፣ዶሮ ፣የተለያዩ የጥሪ እህሎች፣ቅቤ ወዘተ የሚገባበት አስደናቂ ገዳም ነው። ያዉ ለገዳሙ ገቢ ሆኑ ተሸጦ ለካህናት ደሞዝ ይሆናል በአመት ደሞዛቸዉ ለአንድ ከከህን 600ብር ነዉ።
አባቶች እደሚሉት ገዳሙ አካባቢ ወረርሽኞ ያበደ የዉሻ በሽታ እና ከብት በሽታ ሲኖር ታቦቱ ሲወጣ ወረርሽኞ በሽታዉ ይጠፍል።እርሱ ባለቤቱ በሃገራችን የመጣዉን ወረርሽኞ ያጥፋልን ይቅር ይበል።አሜን!
ወዳጆቼ በተለይ ውጭ ያላችሁና መሄድ የማትችሉ ስለት የማትረሱ፨ "አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ"፨ብላችሁ ተሳሉ ንገሩ ወድያው በዕለት ነው ለአዘነ ሰው ሲደርስ ደግሞ ምንም ጥያቄ የለም ስሙን ብቻ መጥራት ወድያው አፋጣኛ ምላሽ የምናገኛበት ገዳም ነው።
ይህንን ገዳም ነሐሴ 13ቡሄ እንድትጎበኛ እንድትባረኩ ይህንን ገዳም የረገጠ ደብረ ታቦርን እንደረገጠ እቆጥርለታለሁ ይላል ቃልኪዳኑ።
በዚህ በደብረ ታቦር በዓል ቀን፤ እንዲሁም ወንድ ልጅ እንደ 40ቀን;ሴት ልጅ እንደ 80ቀን አድርጌ እቆጥራቸዋለሁ ይላል የገዳሙ የቦታው ቃልኪዳን
ጉዞም ገዳሙ ነሐሴ 12ተኬዶ በ13 አክብረን አንግሰን መመለስ።
መነሻ_ነሐሴ 12
መመለሻ _ነሐሴ 13
ለበለጠ መረጃ_
ሀ/0911190212
ለ/0911481388
ሐ/0979986969
መ/0901002929
ወዳጆቼ እርሱ ባለቤቱ እግዚአብሔር አብ ነው ታቦቱ።ለደጁ ለበረከቱ ያብቃችሁ !የውስጣችሁን እንቆቅልሽ ይፍታላችሁ!
ሃገራችንን ሰላም ያርግልን!
ሽታውን ከአለም ላይ ያጥፉልን!አሜን!!!
ገዳሙ እርዳታ ያስፈልገዋል መርዳት የምትፈልጉ እግዚአብሔር የፈቀዳችሁ እርዱ.....

Account no-1000241841317/ደብረ ምህረት አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስትያን/
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ(Commercial Bank of Ethiopia)

ቦታው/_ሰሜን ሸዋ መንዝ መንገድ ከአዲስ አበባ 195ኪሜ መዘዞ ከተማ አቡነ እጨጌ ዮሐንስ ዘፀገሮ ገዳም መውረጃ እንደደረስን ከመዘዞ ከተማ የ1ሰዓት የእግር መንገድ አናዥጋ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ።