2022-06-27 09:24:14
የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ማኅበር፣ ከግል ከፍተኛ ተቋማት የሚወጡ ምሩቃን በአንዳንድ የመንግሥትና የግል ቀጣሪዎች ተቀባይነት እንዳላገኙ አስታወቀ፡፡
ማኅበሩ ይህንን ያስታወቀው ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ረቡዕ ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ውይይት ነው፡፡
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ሞላ ፀጋዬ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ አንዳንድ የመንግሥትና የግል ቀጣሪዎች ከግል ከፍተኛ ተቋማት የሚወጡ ተማሪዎችን አይቀጥሩም ብለዋል፡፡
በተለያዩ የትምህርት መርሐ ግብሮች ተመርቀው በሥራ ላይ የሚገኙ ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የወጡ ሠራተኞችም፣ ‹‹የደረጃ ዕድገት አንሰጥም›› እንደተባሉም አስረድተዋል፡፡
ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተማሪዎችን አንቀጥርም የሚሉ የመንግሥትና የግል ድርጅቶች መኖራቸውን፣ ከእነዚህም መካከል ባንኮችና የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችም መሆናቸውን ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዱ መሆኑን፣ ሌሎችም የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሩ ምሩቃንን አንቀበልም (አንቀጥርም) መባላቸውን ለቋሚ ኮሚቴው ገልጸዋል፡፡
በተለይ በአንዳንድ የክልል ከተሞች ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በትምህርት መርሐ ግብር መሠረት ተመርቀው በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞች፣ የደረጃ ዕድገት እንደማያገኙና የማይቀጥሩ ተቋማት እንዳምሉ ተናግረዋል፡፡
ተመራቂ ተማሪዎችን ከማይቀበሉና ለሠራተኞችም የደረጃ ዕድገት ከሚከለክሉ ክልሎች መካከል አማራና ደቡብ ይገኙበታል ብለዋል፡፡
via tikvahuniversity
https://t.me/jobinfo4searcher
443 views06:24