2022-08-26 16:29:59
#ኢትዮጵያ
የወቅቱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በቀጣይ ላለባቸው የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንትነት ምርጫ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል
ካነሷቸው ነጥቦች መካከል :-
√ ከእኔ በፊት ለነበሩት አመራር ትልቅ ክብር አለኝ ፣ ወደዚህ ሀላፊነት ስንመጣ የሪፎርም ጥናት አድርገን የነበሩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ተሰርቷል ።
√ የብሔራዊ ቡድን ግንባት ላይ ትኩረት ሰጥተን ሰርተናል ።
√ አስራ ሶስት አመት ተዘግቶ የነበረው ካፍ አካዳሚ መጠቀም መጀመራችን ለብሔራዊ ቡድኖቻችን ግልጋሎት ሲሰጥ ከፍተኛ ወጪን ቀንሷል ።
√ የካፍ አካዳሚን አሁን ካለበት በተሻለ ደረጃ ለማዘመን በመጪው አራት ዓመት ሰርቶ ለማስረከብ ዋነኛ አለማዬ ነው ።
√ በቀጣይ የአራት ዓመት ጉዟችንን ገምግመን ተቋማዊ ለውጥ ላይ እንሰራለን ።
√ አሁን ላይ ካለው የተሻለ የስፖንሰር ስምምነት ሊኖረን ይገባል ፣ እኛ ስንመጣ ተቋሙ ከነበራዊ ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታ የሚታወቀው በሽብር ነው ፣ አሁን ላይ ግን በመልካም ነገር ነው ።
√ ይህንን እይታ በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ እና ተጨማሪ ስፖንሰሮችን ለማምጣት በተሻለ እንሰራለን ።
√ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምርጫ ከስፖርቱ ባለፈ #ለሀገራዊ_ምርጫ ምሳሌ እንዲሆን እንፈልጋለን ።
√ ጉባኤው ምን እንደሚሰራ ያውቃል መራጩ 26 ሰዎች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው ያውቃሉ ።
√ የሴቶች ሊግ ፣ ሱፐር ሊግ እና ብሔራዊ ሊግ በቀጣይ የፊፋ ፕላስ ተጠቃሚ እንዲሆን እናደርጋለን ፣ ይህም የምስል መብቶችን ለመሸጥ ይረዳናል ይህንን ለማድረግ ስራዎች ተጀምረዋለል ።
√ ይህን ፕሮጀከት ለመስራት ከጣልያን ተቋም ጋር ከዓመታት በፊት ብንስማማ በወቅታዊው የኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል ።
1.2K viewsedited 13:29