Get Mystery Box with random crypto!

1 ሩሐማ፦ምሕረት ማለት ነው። 2 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል ማለት ነው። 3 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር | Information Science and Technology

1 ሩሐማ፦ምሕረት ማለት ነው።
2 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል ማለት ነው።
3 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር ወዳጅ ማለት ነው።
4 ኑኃሚን፦ደስታየ ማለት ነው።
5 ናትናኤል፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው።
6 አዛሄል፦እግዚአብሔር ያያል ማለት ነው።
7 ኢዮስያስ፦እግዚአብሔር ይደግፋል ማለይ ነው
8 ኢዩኤል፦እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው።
9 በርናባስ፦የመጽናናት ልጅ ማለት ነው።
10 ሶፎንያስ፦እግዚአብሔር ሰውሯል/ጠብቋል ማለት ነው።
11 ሕዝቅኤል፦እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል ማለት ነው።
12 ኬልቅያስ፦እድል ፈንታየ እግዚአብሔር ማለት ነው
13 ሳሙኤል፦እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት ነው።
14 ሚኪያስ፦ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው! ማለት ነው።
15 ሆሴዕ፦እግዚአብሔር ያድናል ማለት ነው።
16 ሔዋን፦የሕያዋን ሁሉ እናት ማለት ነው።
17 ሕዝቅያስ፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው ማለት ነው።
18 መልከጼዴቅ፦የሰላም ንጉሥ ማለት ነው።
19 ሚልኪያስ፦መልእክተኛየ ማለት ነው።
20 ሣራ፦ልዕልት ማለት ነው።
21 ስምዖን፦ሰማ ማለት ነው።
22 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው።
23 ናሆም፦መጽናናት ማለት ነው።
24 ናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
25 አልዓዛር፦እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው።
26 አስቴር፦ኮከብ ማለት ነው፣
27 አቤሜሌክ፦የንጉሥ አገልጋይ ማለት ነው።
28 አቤሴሎም፦አባቴ ሰላም ነው ማለት ነው።
29 አብድዩ፦የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ነው።
30 አብራም፦ታላቅ አባት ማለት ነው።
31 አብርሃም፦የብዙዎች አባት ማለት ነው
32 አኪያ፦እግዚአብሔር ወንድሜ ነው ማለት ነው።
33 አክዐብ፦የአባት ወንድም ማለት ነው።
34 ባሮክ፦ቡሩክ ማለት ነው።
35 አዳም፦መልካሙ ማለት ነው።
36 ኢሳይያስ፦ እግዚአብሔር ደኅንነት ነው ማለት ነው።
37 ባርቅ፦መብረቅ ማለት ነው።
38 ኢያሱ፦እግዚአብሔር አዳኝ ነው ማለት ነው።
39 ኢዮሳፍጥ፦እግዚአብሔር ፈርዷል ማለት ነው።
40 ኢዮራም፦እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ ማለት ነው።
41 ኢዮርብዓም፦ሕዝቡ እየበዛ ይሄዳል ማለት ነው።
42 ቤተልሔም፦የእንጀራ ቤት ማለት ነው።
43 ኢዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
44 ኢዮአቄም፦እግዚአብሔር አቆመ ማለት ነው።
45 ኢዮአብ፦እግዚአብሔር አባት ነው ማለት ነው።
46 ኢዮአታም፦እግዚአብሔር ፍጹም ነው ማለት ነው።
47 ኢዮአካዝ፦እግዚአብሔር ይዟል ማለት ነው።
48 ኤልሳዕ፦እግዚአብሔር ደኅንነት ነው ማለት ነው።
49 ኤልያስ፦እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው።
50 ኤልያቄም፦እግዚአብሔር ያስነሳል ማለት ነው።
51 ኤዶም፦ቀይ ማለት ነው
52 እስራኤል፦ከእግዚአብሔር ጋር ይታገላል ያሸንፍማል ማለት ነው።
53 ኤልሳቤጥ፦እግዚአብሔር መሐላየ ነው ማለት ነው።
54 ኤልሻዳይ፦ሁሉን ቻይ አምላክ ማለት ነው።
55 ሀሌሉያ፦እግዚአብሔርን አመስግኑ ማለት ነው።
56 ሰሎሞን፦ሰላማዊ ማለት ነው።
57 ኬብሮን፦ኅብረት ማለት ነው
58 አዛርያስ፦እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው።
59 ኤደን፦ደስታ ማለት ነው።
60 ዖዝያን፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው ማለት ነው።
61 ዘካርያስ፦እግዚአብሔር ያስታውሳል ማለት ነው።
62 ይሳኮር፦ ዋጋዬ ማለት ነው
63 ይዲድያ፦በእግዚአብሔር የተወደደ ማለት ነው።
64 ዮሐናን፦እግዚአብሔር ጸጋ ሰጪ ነው ማለት ነው።
65 ዮሐንስ፦እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው።
66 ዮሴፍ፦ይጨምር ማለት ነው።
67 ዮናስ፦ርግብ ማለት ነው።
68 ዮናታን፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
69 ዮአኪን፦እግዚአብሔር ያቆማል ማለት ነው።
70 ዮካብድ፦እግዚአብሔር ክብር ነው ማለት ነው።
71 ምናሴ፦ማስረሻ ማለት ነው።
72 ዮፍታሔ፦እግዚአብሔር ይከፍታል ማለት ነው።
73 ዲቦራ፦ንብ ማለት ነው።
74 ዳንኤል፦እግዚአብሔር ፈራጅ ነው ማለት ነው።
75 ጎዶልያስ፦እግዚአብሔር ታላቅ ነው ማለት ነው።
76 ጽዮን፦አምባ ማለት ነው።
77 ጳውሎስ፦ብርሃን ማለት ነው።
78 ሴት፦ምትክ ማለት ነው።
79 ጴጥሮስ፦አለት ማለት ነው።
80 ሄኖክ፦ታደሰ ማለት ነው።
81 ኄራኒ፦ሰላም እና ፍቅር ማለት ነው።

.

1 ሐና፦ጸጋ ወይም ስጦታ ማለት ነው።
2 ሮቤል፦እነሆ ወንድ ልጅ ማለት ነው።
3 ኤርምያስ፦እግዚአብሔር ከፍ ያደርጋል ማለት ነው።
4 ሮብዓም፦ሕዝብ ይብዛ ማለት ነው።
5 ማራናታ፦ጌታ ሆይ ና ማለት ነው።
6 ቤቴል፦የእግዚአብሔር ቤት ማለት ነው።
7 ቄርሎስ፦የተመረጠ ምርጥ ማለት ነው።
8 እስጢፋኖስ፦አክሊል ማለት ነው።
9 ሳውል/ሳኦል፦ከእግዚአብሔር የተለመነ ማለት ነው።
10 ሴዴቅያስ፦የእግዚአብሔር ጽድቅ ማለት ነው።
11 ፊቅጦር፦ኀዘኔን አራቀልኝ ማለት ነው።
12 ንፍታሌም፦ታጋይ የሚታገል ማለት ነው።
13 ዮርዳኖስ፦ወራጅ ውሃ ማለት ነው።
14 ዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
15 ገነት፦የአትክልት ስፍራ ማለት ነው።
16 ፊልድልፍያ፦የወንድማማች ፍቅር ማለት ነው።
17 ዲና፦ፈረደ ማለት ነው።
18 ማኑሄ፦እረፍት ማለት ነው።
19 መልሕቅ፦ከብረት የተሠራ የመርከብ ማቆሚያ
20 ራማ፦ከፍታ ማለት ነው።
21ቴዎድሮስ፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው።
22 ፊላታዎስ፦የአምላክ ወዳጅ ማለት ነው።
23 ሕርያቆስ፦ኅሩይ ምርጥ ማለት ነው።
24 ፊልጶስ፦ወንድም ወዳጅ ማለት ነው።
25 ቶማስ፦ፀሐይ ማለት ነው።
26 ታዴዎስ፦እሸቱ ማለት ነው።(ግብራዊ ትርጓሜ)
27 ማትያስ፦ፀሐይ ወይም ምትክ ማለት ነው።
28 ቀሌምንጦስ፦ግንብ ማለት ነው።
29 አቤል፦በግ ወይም ደመና ማለት ነው።
30 ኖኅ፦ደስታ ማለት ነው።
31 ሴም፦ተሾመ ማለት ነው።
32 ይሥሐቅ፦ደስታ አንድም ይሳቅ ማለት ነው።
33 ሙሴ፦የውሃ ልጅ ማለት ነው
34 አሮን፦የእግዚአብሔር ተራራ ማለት ነው።
35 ጌዴዎን፦እግዚአብሔር ኃያል ነው ማለት ነው።
36 እሴይ፦ዋጋየ ማለት ነው።
37 አሚናዳብ፦መንፈስቅዱስ ማለት ነው።
38 ዳዊት፦የተወደደ ልበ አምላክ ማለት ነው፣
39 ዕንባቆም፦ጠቢብ አዋቂ አስተዋይ ማለት ነው።
40 ሄኤሜን፦ምኞቴን አገኘሁ ማለት ነው።
41 አሞጽ፦እግዚአብሔር ጽኑ ነው ማለት ነው፣
42 ዮናስ፦ርግብ ማለት ነው።
43 ሐጌ፦የእግዚአብሔር መልእክተኛ ማለት ነው።
44 ራኄል፦በግዕት ማለት ነው።
45 ዕዝራ፦ረዳቴ ማለት ነው።
46 ሔርሜላ፦ከክብር ዘመድ የተገኘች ማለት ነው።
47 መርቆሬዎስ፦የአባት ወዳጅ ማለት ነው።
48 ኤጲፋንዮስ፦ምስጢር ገላጭ ማለት ነው።
49 ሜሮን፦የተባረከ ሽቱ ማለት ነው።
50 ሱላማጢስ፦ሰላማዊት ማለት ነው።
51 ሶምሶን፦ፀሐይ ማለት ነው።
52 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው።
53 ማርታ፦እመቤት ማለት ነው።
54 ሊዲያ፦ፈራሂተ እግዚአብሔር ማለት ነው።
55 ኤፍሬም፦ፍሬያማ ፍሬው ማለት ነው።
56 ኤፍራታ፦ክብርት የተከበረች ማለት ነው።
57 ታዴዎስ፦ተወዳጅ ወይም ፍቁር ማለት ነው።(ቃላዊ ትርጓሜው)
58 ኢየሩሳሌም፦የሰላም ሀገር ማለት ነው።
59 ሄኖስ፦ሰው ማለት ነው።
60 ሰሎሜ፦ሰላም ማለት ነው።

ማስታወሻ፦ከላይ ከጻፍኳቸው ውስጥ አንዳንድ ስሞች ከ81ዱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የማይገኙ ከሌሎች የታሪክ እና የገድል መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ስሞች መሆናቸውን ማሳወቅ እፈልጋለሁ።

.
ምንጭ፦የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ የአራቱ ጉባኤያት ትርጓሜ መጻሕፍት