Get Mystery Box with random crypto!

ሂላል ኪድስ Hilal Kids

የቴሌግራም ቻናል አርማ hilaleder — ሂላል ኪድስ Hilal Kids
የቴሌግራም ቻናል አርማ hilaleder — ሂላል ኪድስ Hilal Kids
የሰርጥ አድራሻ: @hilaleder
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.89K
የሰርጥ መግለጫ

ህፃናትን የሚመጥኑ ኢስላማዊ ትምህርቶችና ጠቃሚ መልዕክቶች የሚተላለፉበት አንዲሁም ልጆችን የሚያዝናኑ የተለያዩ ውድድሮች የሚካሄድበት ቻናል ነው።
👉 መጪውን ትውልድ በመገንባት ጉዞ ላይ አብረውን ይሁኑ!!
ለማንኛውም አስተያየት 👇👇👇
@hilalederbot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-28 21:38:11
ሁለተኛው!!
ጨዋታን በቁም ነገር ያዋዛ፣ ሀገራዊ እሴቶች የሚንጸባረቁበት፣ የሀጅ ስርአት በተግባር የሚማሩበት፣ከነቢዩላህ ኢብራሂም(ዐ.ሰ) እስከ ረሱላችን(ሰ.ዐ.ወ) ያለው ታሪክ የሚዘከርበት ፣ለሙስሊም ቤተሰብ የሚመጥን ልዩ የቤተሰብ አረፋ ፌስቲቫልና ኤግዚቢሽን በአረፋ ማግስት እሁድ ሃምሌ 3 እንዳያመልጥዎ!


መጪውን ትውልድ በመገንባት ጉዞ ላይ አብረውን ይሁኑ!
ሂላል ኪድስ ፕሮዳክሽን
829 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 09:34:50 ክፍል 5

የትናንሽ ልጆች ጠብና ግብግብ ውስጥ የተወሰኑ ፋይዳዎች አሉት።
-ሌሎችን ለማሸነፍ አቅም ያላቸው መሆኑን ያውቁበታል፡፡
-ይቅርታን፣ ድል አድራጊነትና (አሸናፊነትን)፣ ሽንፈትን የመቀበል ልምድን ያዳብሩበታል።
-እንደዚሁም ደካማ ጎናቸውንም ይለዩበታል፡፡
-ጠቡ ቀላልና በስሱ ከሆነ ከቤቱ ድብርትን ለማባረር መተራረብና ደስታን ለቤቱ ሊለግሱት ይችላሉ -በጠቡ መሃል በሚገኙ አጋጣሚዎች ለመዝናናትም ይቻል ይሆናል፡፡

ቤት ለልጆች የተለያዩ የህይወት ተሞክሮዎችን የሚለማመዱበት የመሰልጠኛ ማዕከል መሆኑም መዘንጋት የለበትም፡፡
በመሆኑም አንድ ቤት በልጆች መካከል ምንም አይነት ሽኩቻ (ጠብና ንትርክ) የሌለበት መሆኑ አዎንታዊ መልእክት አስተላላፊ አይደለም፡፡

#የልጆች ጠብ ችግር የሚሆነው መቼ ነው?

በልጆቻችን መሀከል የሚኖረው ጠብና ንትርክ አሳሳቢና አስፈሪ የሚሆነው ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱት ሁኔታዎች ይፋ መሆን የጀመሩ እንደሆነ ነው
1. የቃላት ልዩነት (ንትርኩ) ወደ ቦክስ መሰናዘር እና ከባድ ቁጣን የወለደ ከሆነ ወይም ዱላ መማዘዝ በማስከተል በአንደኛው ወገን ላይ የአካል ጉዳት የሚያደርስ ድብድብ ከተሸጋገረ

2. በጠቡ መካከል አስቀያሚ ቃላትን መጠቀም ከጀመሩ

3. ባልተለመደ ሁኔታ ተደጋጋሚ ጠብ ውስጥ መግባታቸው ከታየ

4. ቤተሰቡን ወደ መረበሽና የት/ት ሒደታቸው ላይም ተፅዕኖ ማሳረፍ ከጀመረ

5. በወንድሙ እንደተሸነፈና፣ በደል እንደተፈጸመበት የሚሰማው ወገን መገኘት በተለይ በታላቁ ግፍ ተፈፅሞብኛል ብሎ ታናሽ መብሰልሰል ከጀመረ

አንደኛው ልጅ ዘንድ የብቀላ ስሜት (መንፈስ) እየጎለበተ መምጣቱን ካስተዋልን ጉዳዩ ገደቡን አልፎ ሌላ መዘዝ ከማምጣቱ በፊት የቤተሰቡ ጣልቃ ገብቶ ነገሮችን ለማስተካከል መሞከር የግድ አስፈላጊ ይሆናል፡:

በቀጣይ ስለመንስኤዎቹና መፍትሔዎቹ ይዘን እንመለሳለን
911 views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 18:32:56 ክፍል 4
በልጆች መካከል የሚከሰት ጠብ

የሰው ልጅ በአጠቃላይ ልጅም ሆነ አዋቂ በብቸኝነት መኖር የማይችልና ማህበራዊነትም መገለጫው የሆነ ፍጡር ነው፡፡ ነገር ግን የበርካቶች መሰባሰብና አብሮነት ለተለያዩ የውድድር መንፈሶች መዳረጉ የታወቀ እውነታ ነው ከዚያም አልፎ ክርክር ፣አለመግባባት፣ንትርክና በአጠቃላይ የመልካም ግንኙነት መበላሸት መከሰቱ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፡፡ የዚህ ጉዳይ መሰረታዊ መነሻው ደግሞ በሰዎች መካከል ያለና የሚኖረው የሃሳብ፣ የፍላጎት (ዝንባሌ)፣የአስተዳደግ፤ የጥቅም፣ነገሮችን የምንመለከትበት መነፅር መለያየት ነው፡፡ አንድ ግልፅ መርህ ቢኖር እያንዳንዱ ግለሰብ ለሌላ ግለሰብ ሌላ ሰው የመሆኑ ሚስጥር ነው፡፡ እናም ያ ሰው በዚህኛው ላይ የተለያዩ ምቾቶችን የሚነፍጉ ድርጊቶች በተለያዩ አጋጣሚዎች ሊፈፀምበት ይችላል፡፡ ስለሆነም የማናችንም ቤት ከመጎናተልና ከመጎሻሸም እንደምን ሊወገድ ይችላል። ከላይ የጠቀስናቸው የተለያየ ስብዕና የተበላሱ ሰዎች በአንድ ጣራ ስር ሲኖሩ መነካካት የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የተለመደና ከቁጥጥር ውጭ የማይሆነው ንትርክና ከተለመደው ወጣ የሚል እንዲሁም አሳሳቢና አደገኛ የሆነም አይነት አለ፡፡

#በርካታ ጥናቶች እንዳመላከቱት በወንድማማቾች (እህትማማቾች) መካከል የሚኖር እሰጥ አገባ ከእድሜ መጨመር ጋር እየቀነሰ የሚመጣ ክስተት ነው ለምሳሌ የ 8 ዓመት ህፃናት (ልጆች) ከ 4 ዓመት ህፃናት ያነሰ ጠብ ውስጥ የመግባት አጋጣሚ አላቸው፡፡

በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል ፀበኝነቱ እንደሚበረታም ምሁራኑ አመላክተዋል፡፡
ተቀራራቢ እድሜ ባላቸው ለምሳሌ 5 እና 6 ወይ ከ1 ዓመት ወይም ከዓመት ተኩል እስከ 2 ዓመት ልዩነት ባለበት ትግሉ ይበረታል።
እዚህ ጋር ሊነሳ የሚገባው ነጥብ ግን የትናንሽ ልጆች ጠብና ግብግብ ውስጥ የተወሰኑ ፋይዳዎች ያሉት መሆኑን ነው፡፡

እነዚህ ፋይዳዎች ምን ምን ናቸው የሚለውን በቀጣይ ይዘን እንመለሳለን በአላህ ፍቃድ
957 viewsedited  15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 10:59:26
በሰለዋት ልብ ትዋባለች
በሰለዋት ህይወት ትደምቃለች
በሰለዋት ምድር ታበራለች

صلى الله عليه وسلم
696 views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 22:31:43 ክፍል 3
......ከባለፈው የቀጠለ

#ልጆቻችን ላይ ውሸትን ለማስወገድ የሚረዱን መንገዶች

❖ ልጆቻችን እውነት ከእስልምና (ከሃይማኖት) ትላልቅ እሴቶች መካከል አንዱና ዋናው መሆኑን እንዲያውቁ ማድረግ፡- ልጆች ውሸት እንዴት እንደሚጠላና የተወገዘ ነገር መሆኑንም ማስረዳት ያስፈልጋል፡ ውጤቱም የከፋ መሆኑን ልናመላክት ይገባል፡፡ ረሱል (ሰዐወ) እውነት ወደ በጎ ነገር ይመራል ሲሉ አስተምረዋል፡፡አንዲት ሴት ነበረች ይባላል፡ ስለውሸታሞች የከፋ ፍጻሜ የሚተርኩ ከ20 በላይ ተረቶችን በቃሏ አጥንታለች፡ እናም ሁሌም ልጆችን ስታገኝ ታወራላቸዋለች፡ በዚያም ምክንያት ካሉት ልጆቿ መካከል የ9 አመቱ ልጅ እቤት ውስጥ በስህተት እንኳ ውሸት እንዳይወራ እራሱን ዘበኛ አድርጎ ቀረ፡ ቀልድ እንኳን ሲነሳ እውነት እንዲሆን ያስጠነቅቅ ነበር፡፡(ተጠቀሙበት)

❖ ለልጆቻችን በምንም ምክንያት ውሸት ከቅጣት እንደሚያድናቸው ምልክት አለመስጠት፡- እንዲያውም እውነቱን ሲናገር ቅጣት እንደሚቀንስለትና ለሰራው ስህተት ምህረት እንደሚያስገኝለት ልናስረዳው ይገባል፡ ያ ካልሆነ ቅጣቱ የውሸቱና ያጠፋው ጥፋት ሆኖ እንደሚመጣ እናስረዳው፡

❖ ልጆቹ የዋሹበትን ምክንያት ማወቅ፡- ምክንያቱን አለማወቅ መፍትሄ ለማግኘት ይከብደናል፡፡ቅጣትን ፈርተው ከሆነ ቅጣቱን መቀነስ መልካም ነው፡ ልጁ ደህንነቱ የተጠበቀ መሆኑ እንዲሰማው ማድረግና ነገር ግን ያጠፋውን ጥፋት ዳግም እንዳይፈጽመው ማሳመን ከዚያም እነዚህን ጥፋቶች መደጋገም ሊያስከትል የሚችልውን ውጤት ማስረዳትም የግድ ነው፡ ለውሸቱ መነሻ የሆነው ሌሎችን ዝቅ አድርጎ መመልከቱ ከሆነ የምናስታውሰው ከሰዎች ጋር መልካም ግንኙት መመስረት መቻል እንዳለበት ለዚህ ደግሞ መከባበር የግድ መሆኑን ማስረዳት፡ ልጁ የሚዋሸው የሚዋሹ የቤተሰቡ አባላትን አይቶ መሆኑን ከተረዳን እንግዲህ ከራሳችን ጋር እውነተኛ ሂሳብ መስራት ያስፈልገናል፡ እራሳችንን ለማረምና ለሌሎች መበላሸትም ምክንያት የመሆናችንን ሃላፊነት መውሰድ ይጠበቅብናል፡ ምክንያቱ የዝቅተኝነት ስሜት ከሆነ በራስ የመተማመን መንፈሱን ማዳበርና እና ተጨባጩንም አምኖ እንዲቀበል ማሳመን፡ ያሉትን ጠንካራ ጎኖችን አጉልቶ ማሳየት እንዲያዳብራቸው ማስረዳት በራስ ለመተማመን ይረዳል፡፡

❖ ልጁን ውሸታም ነኝ ብሎ ራሱን እዳይቀበል መጠንቀቅ፡- የቱንም ያህል የዋሸን መሆኑን ብናውቅም፡ ምክንያቱ ነኝ ብሎ ከተቀበለው ስራው (መገለጫው አድርጎ) ሊይዘው ስለሚችል፡ ከኛ የሚጠበቅብን ካለበት መጥፎ አመል ለማላቀቅ መስራት ነው፡ ለምሳሌ ስለእውነተኞች ሲነሳ በጣም ማሞገስና ማወደስ፡ እውነት የተናገረባቸውን አጋጣሚዎቹን በሙሉ ማድነቅና ማበረታታ፡ ሲዋሽ ሲያጋጥመን እንደስህተት በመቁጠር እንዳይደግመው ማሳሰቢያ እየሰጠን ማለፍ፡ የመሳሰሉትን መጠቀም መልካም፡ ነው፡ በርካታ ውጤታማ ወላጆች ልጆቻቸውን ያሳደጉት አዎንታዊ ጎኖቻቸውን በማጉላትና ማበረታታት በመሆኑ ልጆቻቸው ካደጉ በኋላ እንኳ በልጅ ልጆቻቸው ላይ በማየት ተደስተዋል፡፡

በቀጣይ ሌሎች የልጆች የባህሪ ችግሮችን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
1.0K views19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 11:51:13
ጌታችን ሆይ የአንተን የክልከላ አጥሮች ሳንንድ የምንኖር፣ አንተን በፍቅር ከፍታ ላይ ሆነን የምናመልክ ጥንቁቅ ባሮችህ አድርገን። አንተው በፈቀድክልን የእዝነት ዳስ ተጠልለን በፍቅር ውቅያኖስህ እየዋኘን ለሌሎች አረአያ የምንሆን አድርገን፤ በረከቱን አንቧቧልን፤ ለሰውኛው ጎዶሎነታችን ሙላልን።
መልካም ጁምዐ
907 views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 20:56:16 ክፍል ሁለት

#ውሸትን ከልጆቻችን ላይ እንዴት ማስወገድ እንችላለን?

እድሜያቸው አራትና አምስት አመት አካባቢ የሆኑ ልጆች ውሸት መናገራቸው ብዙ አያስጨንቅም፡ ምክንያቱም እነዚህ ልጆች በዚህ እድሜያቸው የገሃዱን እና የምናቡን አለም ልዩነት ብዙ አይረዱትም፡ የሚናገሩት ከተጨባጩ አለም ጋር ይሄዳል አይሄድም ብሎ ለመመዘን የሚያስፈልገው ክህሎት ገና አልዳበረላቸውም፡፡

ልጆችህን ጠባብ ክፍል ውስጥ ወስደህ የወንጀል ምርመራ ስራ አትስራ ማለትም ይህን ይህን ሰርተሃል እመን እያልክ አታስፋራራ፡ ማስረጃ ባጣህለት ነገር እራሱ ላይ መስክሮ እንዲቀጣልህ አትፈልግ (ጥፋት አጥፍቶ ሊሆን ይችላል ግና በዚህ መንገድ ለማሳመን መሞከርህ ውጤታማ አይደለም)፡፡

#ልጆቻችን ላይ ውሸትን ለማስወገድ የሚረዱን መንገዶች

❖ ልጆቻችን በራሳቸው እንዲተማመኑና ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን የኑሮ ሁኔታ አምነው እንዲቀበሉ ማድረግ፡-

አንዳንድ ጊዜ ህጻናት ለራሳቸው ክብርን ወይም የሆነ የጎዳላቸውን ነገር ለመሙላት ብለው ሲዋሹ ይገኛሉ ይህን የሚያደርጉት ያለባቸውን የዝቅተኝነት ስሜት ለማጥፋት እና እኔ ትልቅ ነኝ ጠቃሚ ሰው ነኝ የሚል መንፈስን ለመላበስ ነው፡ ለምሳሌ ብዙ ህጻናት አባቶቻቸው ሃብታም እንደሆኑ ለማሳወቅ ውድ ነው ብለው የሚያስቡትን ንብረት አለን ይላሉ፡ ይህ ቤታቸው ውስጥ ያለውን ድህነት ለመደበቅና ድሃ ነን የሚለውን ስሜት ለማስወገድ የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው፡፡

❖ ቤት ውስጥ እውነትን ብቻ መናገር እና ስለ እውነት መሞገት፡-

አባት እናትን፤ታላቅ ወንድም ታናናሾቹን፤ሴቶቹ ጓደኞቻቸውን በሚዋሹበት ቤት የሚያድግ ህፃን በምንም ምክንያት ውሸትን እንዲተው አይጠበቅበትም የቤቱ ባህል ሆኗልና፡፡ስለሆንም እውነትን ብቻ በመናገር ልጂ ውሸትን አነውሮ እንዲመለከት ይረዳዋል፡፡

❖ በጣም የተጋነነ ውሸት (ወላጆች ስለስራቸው ሁኔታ አጋኖ አለማውራት) ፡-

አንድ ወጣት እንዲህ ሲል ያወራል፡ እናቴ ስለአባቴ ስራ ለጓደኞቿ ስታወራ እሰማለሁ ፡ የሚሰራው እጅግ ቁልፍ የሆነ የሀገሪቱ መስሪያ ቤት ውስጥ በመሆኑ ተደጋጋሚ ፊልድ ይወጣል ትላለች፡ እኔም ት/ቤት ለማገኛቸው ጓደኞቼ እሷ ያለችውን እላቸው ነበር፡ በዚያም ሲቀኑብኝ አስተውላቸው ነበር፡ ልክ ሁለተኛ ደረጃ ስጀምር አንድ ቀን ከባድ አደጋ ወደቀብኝ አባቴ የአንድ ኢንቨስተር ተላላኪ ሆኖ ከዚያ ሰው ጋር ላይ ታች የሚል እንጂ ሌላ አለመሆኑን ስረዳ ይላል፡፡

ቀሪዎቹን መፍትሔዎች በቀጣይ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
962 views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 00:24:35 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

#ዋና_ዋና_የህጻናት_የባህሪ_ችግሮች!
ክፍል አንድ

=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=

ውሸት

ሕጻናት ከሚገጥማቸው ችግሮች መካከል ዋናውና የመጀመሪው ውሸት ነው፡በአሁኑ ሰዐት ውሸት ከህፃናት አልፎ በአዋቂዎች ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እንደወረርሽኝ እየተስፋፋ ይገኛል፡፡ይህ የሚሆነው የሰው ልጆች ለዱንያ ያላቸው ጉጉትና ፍቅር ድንበር ሲያልፍ፤ የማህበራዊ ህይወት ምስቅልቅል መብዛት፤ በተለይም የድህነት መስፋፋትና የእለት ጉርስን ማግኘት ሲከብድ ውሸታሞችን መብዛት ብንጠብቅ አይገርምም፡እናም አንድ ህብረተሰብ እውነተኛና ትክክለኛ ስልጣኔ ለመገንባት ከፈለገ ከእውነተኛነትና ውሸታምነት ጋር ያለውን ቁርኝት ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

#ውሸት_ምንድን_ነው?

አብዛኛውን ጊዜ ውሸት የሚፈጠረው ከሆነ ወንጀል(ስህተት) ወይም ማድረግ ያለብንን ስላላደረግን ወይም የሆነ ነውርን ለመደበቅ ሲባል ነው፡፡ ይህም ማለት አንድ ሰው በፈለገው መንገድ ይሁን የሚሰራውን ሰርቶ ለመደበቅ የሚችልበትና ለሰራው ስህተት የእጁን እንዳያገኝ የሚያስቸል ግርዶ ነው፡፡እናም ውሸት ላይ መዘውተር ማለት ለሁሉም መጥፎ ስራዎች በር መክፈት እንደሆነ ይታመናል፡፡

ስለህጻናት ውሸት ስናወራ ደግሞ ልጆች አንድ ከተከሰተ ነገር በተቃራኒ ሲናገሩ ዋሹ ብለን እንላለን:: ያም እውነታውን ለመደበቅ አልያም ሌሎችን ለማሳሳት ብለው የሚናገሩት ንግግር ሲኖር ነው፡፡

#የውሸት_አደገኛነት!

በማታለልና በውሸት እንዲሁም ቅጥፈት መካከል ጠንካራ ትስስር አለ፡፡ ዛሬ በአለማችን በሚከሰቱ ወንጀሎች ዙሪያ የተደረጉ በርካታ ጥናቶች እንዳመለከቱት ውሸታሞች በአብዛኛው ሌቦችና አታላዮች መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ውሸት እንደባህሪ ያለበት ሰው ማታለልና መስረቅም አብረውት የሚገኙት ባህሪያቶቹ ናቸው፡፡ እናም ይህ ጥምረት የሚገርም አይሆንም ፡ ምክንያቱም ከሃዲዎች እውነታን፤ መርህንና ቃልኪዳንን ጭምር የሚክዱ ሰዎችን ካየን ይህ ባህሪያቸው የተፈለቀቀው ከውሸታምነታቸው መሆኑን እንረዳለን፡፡

ከዚህ በመነሳት የአላህ መልእክተኛ በቃልም በተግባርም ውሸትን አጥበቀው የመታገላቸውን ሚስጥር እንረዳለን። ይህን ያደረጉት በህጻናትም በአዋቂዎችም ላይ ነበር። አብደላህ ኢብኑ አማር የሚባል ሰሃባ እንዳወራው አንድ ቀን እናቱ ጠራችውና የሆነ ነገር እሰጣሃለው አለችው፣ ነቢዩም ምንድን ልትሰጪው ነው ሲሉ እሷም ቴምር አለች፣ እሳቸውም ምንም ባትሰጪው ይህቺው ንግግርሽ ውሸት ተብላ ትመዘገብብሽ ነበር አሏት፡፡

አኢሻም (ረ.ዐ) እንዳስተላለፈችው፡ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዓ.ወ) ከቤተሰባቸው በአንዱ ላይ ውሸትን ካዩበት ያ ሰው አምኖ ተውበት እስኪያደርግ ድረስ አያናግሩትም ነበር፡፡ ይህ እንግዲህ የሚያሳየን ግልጽ አቋማቸውን ነው። ውሸት ካለበት ሰው ጋር ንክኪ የላቸውም በተግባርም በኩርፊያና በመለያየት በዚያ ሰው ባህሪም ላይ ያላቸውን ግልጽ ቅሬታ በማሳየት ዳግም ወደዚህ መጥፎ ስነምግባር እንዳይመለስ በተግባር ያስተምሩ ነበር። ይህም አሳዳጊዎችና ወላጆች ልብ ሊሉት የሚገባ መልካም አርአያነት ነው፡፡

#ህጻናት_ለምን_ይዋሻሉ?

በመጀመሪያ ልብ ልንለው የሚገባ ነገር ውሸት እዚህ አለም ከመጣን በኃላ በትምህርት፤ ከሌሎች በማየትና ከህይወት ተሞክሮዎች የምናገኘው ማህበራዊ ክህሎት እንጅ በተፈጥሮ የሚወራረስ ባህሪ አለመሆኑን ነው፡፡በአንድ ቤተሰብ አባላት ውስጥ የውሸት መስፋፋት የሚጠቁመው እዚያ ቤት ወይም ማህረሰብ ውስጥ ያሉ ሰዎችን ዝቅተኝነትና ዋጋ ቢስነት ነው።

በአዎንታዊ መልኩ ህጻናት በሁለት መሰረታዊ ሁኔታዎች ለውሸት ተጋልጠው ልናገኛቸው እንችላለን፦

የቋንቋ አቅማቸው፡-
የልጆች የቋንቋ አቅም የሚፈቅደውን የቃላት ብዛት በመጠቀም የሚፈልጉትን ነገር ሊናገሩ ይችላሉ። ይህም ፍላጎታቸው ከእውነታው ጋር ምን ያህል ይጣጣማል የሚል እሳቤን ላያካትት ይችላል፡፡

የምናብ ግጥምጥሞሽ መከሰት፡-
ሁኔታወችን በራሳቸው ምናብ በማገጣጠም እውነት ያልሆነን ነገር ሊናገሩ ይችላሉ፡፡
ነገር ግን በአሉታዊ አንፃር ስናየው ህጻናትን ወደ ውሸት የሚገፋፉ ዋና ዋና ምክንያቶችን እናያለን፡

1. ቅጣትን በመፍራትና የምፈልገውን ነገር እከለከላለሁ በሚል ፍርሃት መዋሸት

2. ወላጆችና አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን ለማሳመንና ያጠፉትን ጥፋት እንዲቀበሉት ለማስገደድ ጉልበትንና ቅጣትን በተገበሩት ቁጥር ልጆች እራሳቸውን ለማዳን ሲሉ መዋሸት

3. በአድማጮቻቸው ለመደነቅ ወይም ትኩረትን ለመሳብ

4. የሆነን ነገር ለማግኘት ብሎ መዋሸት (ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲሉ ከትምህርት ቤት አምጡ ተብለናል በማለት ገንዘብ መቀበል ሊሆን ይችላል)

5. ከራሳቸው ላይ አደጋን ለመከላከል ሲሉ እርስ በርስ ሊውሻሹ ይችላሉ

6. ከወላጆች በመቅዳት የነሱን ባህሪ መያዝ፡- የሚዋሹ ህጻናት ብዙውን ጊዜ የሚዋሹ አባቶቻቸውን ወይም እናት ወይም ታላላቅ እህትና ወንድሞቻቸውን ኮፒ አድርገው እናገኛቸዋለን፡ አንድ ወጣት ይህን አስመልክቶ ሲናገር አባቴ ሲሰራና ሲናገር የማየው ነገር በሙሉ ትክክልና እውነት ይመስለኝ ነበር፡ ውሸትን የተማርኩት ከአባቴና እናቴ ነው፡፡በአንድ ወቅት እኔ እንድተኛ ብለው እነሱ እንደተኙ ያስመስላሉ ከዚያ ስተኛ ተነስተው የሚሄዱበት ይሄዳሉ አንዴ እናቴ እንዲህ አለችኝ ይላል ተነስ መጫወቻ ቦታ ልውሰድህ ብላ በጣም ደስ ብሎኝ እየሄድን ስንደርስ እራሴን የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ወንበር ላይ አገኘሁት ይላል፡፡

=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=

በቀጣይ ልጆቻችን ላይ ውሸትን እንዴት ማስወገድ እንችላለን የሚለውን እናያለን በአላህ ፍቃድ፡፡
862 viewsedited  21:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 09:00:41
ብዙዎች በሰው እጅ ይገላበጣሉ፤ እልፎች በግልኮስ ያድራሉ፤ ቢሆንም አፍያውን ተችረው ለጌታቸው ሱጁድ ማድረግን ይናፍቃሉ። እኛ ግን ሙሉ አካል ከሙሉ ጤና ጋር ተችሮናል ለዚህች ኒዕማ ብቻ አላህን ያለምንም ማቋረጥ ቀንና ለሊት ብናመሰግነው ቢያንስበት እንጂ አይበዛበትም።
በጤና የተሞላ፤በምስጋና የታጀበ ውብ ጁምአን ተመኘን።
ጁምአችንን በከህፍ፣በሰለዋት፣በዱአና በዚክር እናስውበው።
መልካም ጁምአ
735 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 19:12:40 ዋና ዋና የህጻናት የባህሪ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው

የህጻናት የባህሪ ችግሮችን ስናነሳ በርካታ እሮሮዎች ከወላጆችና ከአሳዳጊዎች እንሰማለን፡ ችግሮቹ ብዙዎች ቤት መከሰታቸው እንዳለ ሆኖ ችግሮቹን መረዳትና መፍትሄ መስጠቱም ቀላል አልሆነም፡ እንዲያውም ከአለምና ከአካባቢያችን ነባራዊ ሁኔታዎች ፈጣን ለውጦችን ተከትሎ የበለጠ እየተወሳበብን መፍትሄ ለማግኘትም እየከበደንና ከልጆቻችን ጋር መግባባትና ለሚያሳዩት ያልተገቡ ስነምግባሮች መልስ መሰጠት እንዳቃተን በበርካታ አጋጣሚዎች እየገለጽን እንገኛለን፡፡ ስለሆነም ይህን ተከታታይ ትምህርታዊ መጣጥፍ በልጆቻችን ዋናዋና የባህሪ ችግር አይነቶች፤ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ሳደርግ የሚከተሉትን ነጥቦች ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡
በመጀመሪያ አካላዊም ሆነ ስነልቦናዊ ችግር አለበት ለማለትና ጥሩ ስነምግባር አለው በምንላቸው ልጆች መካከል የሚታይና ግልጽ ልዩነትን ማስቀመጥ ከባድ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ባሕሪያትን ኖርማል (ጤናማ) ከሚባለው ልኬት አልፎ መቼ መጥፎና ልናርመው የሚገባው ደረጃ ላይ መድረሱን መለየት ይከብዳል፡፡ እነዚህን ችግሮች ለማወቅ ሁለት መንገዶችን ልንጠቀም እንችላለን፡
የባህሪው ፍጹም ወጣ ማለት፡-በወንድም ወይም በእህቶቻቸው ላይ አደጋ ማድረስ፤ ከፍተኛ የምግብና የእንቅልፍ እጦት፤
የባህሪው መደጋገም፡-ምንም ጉዳይ ላይ ትኩረት ማድረግ አለመቻል፤ብዙ ምግብ በተደጋጋሚ መብላት፤ቅጥ ያጣ እራስ ወዳድነት ማጎልበት፤እንግዶችን በጭራሽ ለማግኘት አለመፈለግ፡ (መታየትን መፍራትና መደበቅ) ወዘተ

ሁለቱንም ምክንያቶች (የችግሩ መጉላትና መደጋገም) በአንድ ላይ ባይከሰቱና በሆነ አጋጣሚ የተከሰተ ከሆነ ብዙ አያሳስብም፤ እንኳን ህጻናት አዋቂዎችም ከመሰል ስህተቶች አይወገዱምና፡፡ ልጁ መደበኛ (የተለመደ) ከሚባል ባህሪ ውጭ ከሆነብን በተቻለ መጠን በአካባቢያችን የሚገኙ የህክምናም ይሁን የስነልቦና ባለሙያዎችን ምክር መጠየቅ አስፈላጊና ተገቢም ነው፡ ካልተገኙ ከኛ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸውን ወላጆች ማማከርም ይቻላል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በኋላ በምናነሳቸው ትምህርቶችና ወላጆች በሚያደርጉት ንባብ እና ክትትል መቼ የባላሙያዎችን ወይም የጎረቤትም ይሁን የወዳጅ እርዳታ እንደሚያስፈልግ ግልጽ  እየሆነ ይሄዳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡
ሌላው ባህሪንና የተለመዱ ስረአቶችን ለመቀየር በምንሞክርበት ጊዜ የሚገጥሙን ችግሮች አሉ

የችግሩ ሰለባ የሆኑት ልጆች ለመፍትሄዎች ያላቸው መልስ (ሪአክሽን) ላይ ያለ ልዩነት
በወላጆችና አሳዳጊዎች መካከልም ያለ የእውቀትና የመረዳት  ደረጃ መለያየት
አንድ የመፍትሄ ሃሳብ ለአንድ ልጅ ሲሆን ለሌላኛው ምንም ፋይዳ አለመኖር፤አንዳንድ ጊዜ ወላጆች ባለሙያዎችን ሊያማክሩ ይሄዱና እንደመፍትሄ የሚነገራቸውን በሙሉ ሞክረውት ግን ጥቅም ሳይሰጣቸው እንደቀረ ወይም ደግሞ ያንን ሃሳብ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመሩ በኋላ ልጁ እንደባሰበትም የሚናገሩ ያጋጥማሉ፡፡
ልጆች እያደጉ ሲመጡና ማህበራዊ እውቀታቸው እየዳበረ ሲመጣ ሊቀንሱ የሚችሉ ባህሪያቶች ላይ የወላጆች ታጋሽ አለመሆን፤ ለምሳሌ
o ትእቢተኛነት
o በቶሎ መናደድ
o የተወሰኑ ምግቦችን በፍጹም አለመመገብ
ነገር ግን አብረው ሊያድጉ እንዲሁም በጊዜ ሂደት እየተባባሱ ሊመጡ የሚችሉ እንደውም በጊዜ መፍትሄ ካልተፈለገላቸው ወደፊት በልጆቹ ስብዕና ላይ ከፍተኛ የሆነ ተፅእኖ ሊፈጥሩ የሚችሉ ባህሪያቶች እንዳሉ መረዳት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ለምሳሌ 
o አንዳንድ ቀላል የሚመስሉ የጤና ችግሮች ለምሳሌ አልጋ ላይ መሽናት፤
o በጣም ተደባዳቢ መሆን (ወላጆች ስርዐት  ማስያዝ እስከሚያቅታቸው ድረስ)
o የወንድሞቹን ንብረት ማጥፋት መሰባበር፡ ማስቸገርና ከቁጥጥር ውጭ መሆን
ስለሆነም መጀመሪያውኑ በቤቱ ነገሮችን ስረዓት የሚያስይዝ ሰው መኖሩን እንዲገነዘብና ህግ እንዲያከብር፤ ለህገ-ወጥ ድርጊቶቹም ሀላፊነት እንዳለበት መማር ያስፈልገዋል፡፡
በቀጣይ በዋና ዋና የልጆች የስነባህሪ ችግሮች፤ ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸውን ይዤ እመለሳለሁ፡፡
 
786 views16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ