ጨካኙ አባት ሴት ልጁ እንዲህ ትላለች .... " 6 አመታትን ያህል አባቴ ባልገባኝ ምክንያት ለትዳር ጥያቄ የሚያቀርቡልኝን ወንዶች ሁሉ እንቢ አለ ። በዚህም ጉዳይ ምንም አይነት ውይይት አይቀበልም ። እኔን ፍለጋ በሩን የሚያንኳኩ ሰዎችን ሁሉ አባቴ በእንግዳ ማረፊያው ክፍል ለግማሽ ሰዓት አንዳንዴም ከዛ ያነሰ ያህል ያወራቸዋል ፣ ከዚያም የመጣው ወጣት በፍጥነት ይወጣል እናቴ አባቴን ለመጠየቅ ቸኮለች" ምንድን ነው የሆነው " እንዲህ ሲል መለሰላት፡- ጥሎሹን አልወደድኩትም የእሱ አቻ በቤታችን ውስጥ የለችም ! የመንፈስ ጭንቀት ወደ እኔ ዘልቆ መግባት ጀመረ ። አባቴ በኔ ድርሻ እና በኔ ደስታ መጋረጃ በመሆኑ በሱ መቆጣት ጀመርኩ። ራሴን እጠይቅ ነበር "እንዴት ሊሆን ይችላል? ለገንዘብ ብሎ ለአንዲት ሴት ልጁ የማይቻለውን ጥሎሽ ይመኛል ! አሁን ተዓምር ተፈጠረ ። አባቴ ከአመልካቾች ከአንዱ ተስማማ ። ባለቤቴ ስለከፈለልኝ ጥሎሽ አባቴ ሳይነግረኝ ትዳራችን ተፈፀመ... የሚገርመው ነገር ባለቤቴ በአማካይ የኑሮ ሁኔታ ላይ ያለ እንጂ ቀድመውት ከጠየቁት ሰዎች አንፃር ከብዙዎቹ ድሃ ነበር እሱም ከአባቴ ጋ ስለተስማሙበት ጥሎሽ (መህር)አልነገረኝም በትዳራችን አስር አመታት አለፉ ። ከባለቤቴ ምንም ክፉን ነገር አላየሁም። ያየሁት ርህራሄን, ደግነትን እና ስስትን ብቻ ነው ዕድሜዬ እየጨመረ ቢሆንም በባለቤቴ እንክብካቤ ምክንያት ምንም የመከፋትም የመረበሽ ስሜት አይሰማኝም ነበር ። አባቴ ጥሎን ወደማይቀረው ጉዞ እስኪሄድ ድረስ.. ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ በኋላ ባለቤቴ ወደኔ መጣ ወደ ደረቱ አቀፈኝና “ትንሿ አትዘኚ " አለኝ ። " ትንሿ " በምትለው ቃል በጣም ተገረምኩ ። በስስት አየኝና ... ‹‹አዎ ትንሼ ነሽ ። ..... ለጋብቻ አንቺን ስጠይቅ አባትሽ ምን ማድረግ እንደምችል ጠየቀኝ። ትንሽ አሰብኩና ፡- አጎቴ ብዙ ምሰጠው የለኝም ። ግን ምዬ የምነግርህ ነገር ቢኖር አንተን በሞት ብታጣህ እንኳ የቲምነት እንዳይሰማት አደርጋለሁ። ልክ የአብራኬ ክፋይ እንደሆነች ሴት ልጅ እንከባከባታለሁ " አልኩት ። አባትሽም ፈገግ አሉና ፡- "ሚስትህ ልጄ ናት"አሉኝ @heppymuslim29 2.6K viewsɯɐɥlǝ, edited 10:54