የባለ ታሪኳ ዘመድ እንዲህ ትላለች ...
" የአክስቴ ልጅ ናት ፣ ሰላሳዎቹን ገብታለች ። እንደየትኛዋም ሴት ሁሉ የትዳሯ መዘግየት አሳስቧታል ። ታድያ እናቶች በሰፈራቸው ለዚህ አይነቱ ክስተት ዱዓ መቀማመጥ ልምድ አላቸው ። ለሷም ዱዓ ይዘውላታል ።
" ያ ረብ ኢማን ያለውን ፣ ዐመለን ሷሊሑን ...!" እያሉ ከተያያዙት ሰንበትበት ብለዋል ።
የባርያውን ልመና ሚቀበለው (አልሙጂቡ) ፣ ድምፁን ሰሚው (አስ-ሰሚዑ) ምላሽ ሰጣቸው ። ገራሚው ነገር ታድያ በስንት ዱዓ የመጣው ባል እዛው ከጎረቤት ይኖር የነበረ ሰው መሆኑ ነው ። በስራ ሌላ ሀገር ነው ሚኖረው ። እሱም ምትሆነውን በመፈለግ ውስጥ ነበር ። ከብዙ መንከራተት ኋላ ውሳኔውን እዚህችው ሴት ላይ አሳረፈ ።
የኒካሁ ዕለት የሁለቱም ጎረቤት የነበረች ተጫዋጭ ሴት ወደሱ ጠጋ ብላ ...
" ምነው እዚሁ አጠገባችን ሆነህ ነው ብዙ ዳቦ ያስጨረስከን? ! " አለችው ።
እናም ...
አጠገባችሁን ተመልከቱ ፣ ከጎናችሁ ጀምሩ ፣ ዙርያችሁን በደንብ ቃኙ
የተባረከውን ይስጠን ፣
የሰጣችሁን አላህ ያቆይላችሁ !
https://t.me/hanan_islamic_paje