የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
2.15K
የሰርጥ መግለጫ
የሰው ልጅ ልብ ነው የገጣሚ ሀገር...!
@Run_Viva_Run
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-09-01 21:46:03
#MAKI
ERMI HAMER DANCE CROW
@Natanimaye
@Natanimaye
@Natanimaye
Join
62 viewsMåki Mårli, 18:46
2022-08-31 21:49:38
https://t.me/yekaldebdabewoch
82 viewsKal--kidan, 18:49
2022-08-31 21:39:29
https://t.me/joinchat/AAAAAEgA0BavjNg50pdX6g
68 viewsMåki Mårli, 18:39
2022-08-30 22:15:01
87 views#lij werkneh, 19:15
2022-08-30 21:48:22
https://t.me/yekaldebdabewoch
103 viewsKal--kidan, 18:48
2022-08-28 17:36:16
እኛእኛ እኮመሬት ሊያበቅል....አሳርሶን
ዝናብ ከላይ....አረስርሶን
ለ.ም.ነ.ት.ን....ሰጥቶ አውርሶን
የተፈጥሮ....ካባ አልብሶን
የምንፋጅ....ጥጋብ ወርሶን
አይ እኛ
እኛ እኮሰበዝ መዘን....መሶብ ሰፍተን
በምጣዱ....እንጀራ አስፍተን
እየበላን....ላንቋደስ
በሞት ማልደን....ላንጓረስ
የቀለለን....ደም መፋሰስ
አይ እኛ
እኛ እኮበአዲስ ዓመት....በአዲስ መንፈስ
ጊዜ ሰጥቶን....ለመታደስ
አበባ አየሁ....ለምለም ሳንል
እንቁጣጣሽ....ሳንዘምር
ጥቅምት እሸት....ሳንከምር
ተዘንግቶን
በክፉ ዐይን የሎስ ዓይቶን
ከአዲስ ዘመን....ላደረሰን
አዲስ ጀንበር....ላወረሰን
ብርሃን ፀጋ....ላለበሰን
ምስጋናችን....ሰማይ ሳይደርስ
የምንፋጅ....በእብሪት ደንደስ
እይ እኛ
እኛ እኮበደብሩ....በመቅደሱ
ምስጢራትን....የዳሰሱ
የሼህ ዱአ....በመስጊዱ
ከአምላካቸው....የማለዱ
ከአባቶች....እምነት ወርሰን
በፀበሉ....ተፈውሰን
በዘምዘሙ....ሽረት ይዘን
መቆም ስንችል....አድረን አንሰን
አንሰን...
አንሰን...
አንሰን...
አንሰን...
ድህነት...ማቅ...ያለበሰን
የአረር...ጥይት...የጠበሰን
አይ እኛ
እኛ እኮበአበባ....ምድር ቀልማ
በቢጫ አደይ....ተሸልማ
እዩኝ. እዩኝ. እዩኝ....ስትል
ቂም በቀልን....የምንፈትል
በልብ ይዘን....የክፋት ትል
ስንባዝን....ስንባትል
አይ እኛ
እኛ እኮቄጠማችን....ከመስክ በቅሎ
የምናጭድ....ሙጃ ሰርዶ
ቅዠታችን....ባህር ማዶ
ሽንቁር ጋኖች....ሁሌም ባዶ
''ለምን?''....ብለን 'ማይሰማን
"እንዴት?" ማለት....የማይቀናን
የንፋስ ውል....ያበጃጀን
የአመል እሳት.....የሚፈጀን
አይ እኛ
እኛበመሳቂያ....ከንፈር ነክሰን
በማያችን....ዕንባ አፍስሰን
ላንራመድ....ሁሌ አንክሰን
በእጃችን....ተተኳኩሰን
ላናሸንፍ....ላንሸነፍ
መገፋፋት....መኮራረፍ
መጠላላት....መጠላለፍ
በሞት ተራ....ልንሰለፍ
አይ እኛ
ኖርናት መቼም...
ክፉ አንቀልባ....እየሰፋን
ማሪያምዬን....እንዳስከፋን
ለሞታችን....ጦርን ቀርፀን
አላህዬን....ሳንማፀን
እየሱሴን....ሳንለምንም
አፈር ገባን....እንደ ምንም
አ........ይ እ..........ኛ አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
ለዚህ ግጥም ፅሁፍ መነሳሻ እንዲሁም በፅሁፉ መጨረሻ ያሉ ለአንዳንድ ሀረጋት ጭማሪ የሆነኝ የ
አስታወሰኝ ረጋሳ "እኛ እኮ" የሚል አንድ የመድረክ ስራ ነው።እናም ምስጋናውን ባለበት
@HAKiKA1
@HAKiKA1
390 viewsአብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ), 14:36
2022-08-27 12:52:07
(እኛ)
ለካብነው ፍቅራችን
አመል እያከፋን፤
ለቆለልነው እምነት
እልህ እያጋፋን፤
ለልብ ኪዳናችን
በጣም ተንቦራቆ
እውነት እየሰፋን፤
እንኳን መፈቃቀር
መጣላቱም ጠፋን!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@HAKiKA1
@HAKiKA1
457 viewsአብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ), 09:52
2022-08-27 08:32:11
https://t.me/+cSe9DcGnHFg3MzY0
በዚህ ቻናል ላይ ስለሚለቀቁ ማንኛውም አይነት የጥበብ ስራዎች ላይ ሀሳብዎትን ለማንሸራሸር ማስፈንጠሪያ linkun በመጫን join ብለው ግሩፑን ይቀላቀሉ
444 viewsአብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ), 05:32
2022-08-25 10:30:16
ዕንባዊ መሰረት
"""""""" """""""""
እንደ እሳት ተቀምጠሽ
በውበት ነበልባል ሆነሽ ከበላዬ፤
በመፋጀትሽ ልክ
እንባዬን ባነባ
"የወንድ ንፍርቅ" ብለሽ ተሳለቅሽ በእንባዬ!
(
አይ አንቺ)
እሳት አንቺነትሽ
በሻማ እኔነቴ ከበላዬ ሲውል፤
አዘቅዝቄ ሳለቅስ
አልገባሽም ከቶ የመነፍረቄ ውል!
(
አየሽ)
ሻማ ያነባውን
ላለመንገዳገድ
ከመቅረዙ አፍሶ ረግጦ ነው የቀና፤
የኔንም ተመልከች
በእንባ መሰረት
ስብርብር ጉልበቴ ጠንክሮ ሲፀና...
(
አየሽ)
የሰው ልጅ ሲያለቅስ
አቅመ ቢስ
ልፍስፍስ
አስመስሎ በሰው ማየት ቢያስለምድም፤
በሀዘኑ ፀንቶ
በእንባው የቆመ ሰው
ከጊዜ በኃላ አይንገዳገድም..!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@HAKiKA1
@HAKiKA1
561 viewsአብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ), 07:30
2022-08-22 19:33:24
ስምና ኩነኔ
"""""""""'''''''
ለውሸትሽ ድጋፍ፥
በ.ማ.በ.ል.ሽ አፋፍ፥
እውነትን ቀብተሽ
በማስመሰል አንባ፥መዝለቅሽ ቢሰምርም፤
ስም ያለው ሞኝ ነው
'ክህደት' ባልኩኝ ቁጥር፥"ወይታሽ" አይቀርም...
አይቀርም
አክብሩልኝ ካለው
ከአስርቱ ትዕዛዝ፥ህግጋት ተላልፎ፤
እንዳትነኩ ካለው
ገነት ከፀደቀው፥እፀ በለስ ቀጥፎ፤
የውሸት ቅኔ ዘርፎ...
የሰው ልጅ በድክመት
በህይወቱ ምላስ፥ኃጥያትን ቢቀስም፤
ዘላለም አለሙን
"እመት'' ሲል ይኖራል
ተደባልቀውበት፥መኮነኛው ከስም!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@HAKiKA1
@HAKiKA1
734 viewsአብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ), 16:33