Get Mystery Box with random crypto!

ካሊድ (ሀበሽስታን) አንድ አንድ ሀሳቦች 1 ሰርከም ሰርከም እያልኩ ከላይ  የት አባህ ማን በዚ | ሀበሻዊ ጥበባት

ካሊድ (ሀበሽስታን)

አንድ አንድ ሀሳቦች 1

ሰርከም ሰርከም እያልኩ ከላይ  የት አባህ ማን በዚህ ሰዐት ውጣ አለህ እያለች መዐቱን ከምታፈላዋ ፀሀይ ሽሽት አንድ እጄን እንደ አቅጣጫ ጠቋሚ ከግንባሬ ትይዮ ቀስሬ…………  ከታች ይሄን የጥቁር አስፖልት ወበቅ ለመዝለል በሚመስል ሳልረግጥ እየተራመድኩ ……ከጐን እና ከጐን መኪና ማየት ተስኖኝ መራመድ የተሳነው ወይም መኖር የተሳነው ከመሆን ለጥቂት አፈተለኩ።

ስለ ፀሀይዋ ሲነሳ አጃዔብ ያሰኛል ወደ ማደሪያዋ ገብታ እንኳን (ግን የት ነው የምታድር ስታድርም ሌላ የምታቃጥለው አዳሪ ወይም ዋይ ይኖር ይሆን? በማታ እንኳን ስለሷ ወግ ከተወጋ ላብ ያጠምቀኛል(በአዲስ አበባ ፀሀይ የማያልበኝ ምላሴን ብቻ እንደሆነ በቅርብ ያጠናቀርኩት ጥናቴ ይናገራል) እንደ ቀኑ የእጅህን መዳፍ ተከልል ተከለል ይለኛል።

አሁን አሁንማ ልምድ ሆኖብኝ ብብቱን እንደተወጋ አምሽቶ ገቢ እጄን ሰቅዬ መዞር ጀምሪያለሁ በቅርብ እንደውም ኮፍያ አድርጌም ከልምዴ የተነሳ መዳፌን ከልዬ ስሄድ አንድ ወታደር ሲቪል ለባሽ አለቃው ጋር በምን እንደተመሳሰልኩበት እንጃለቱን ሰላምታ ሰጥቶኝ ሄደ ፀሀይ አስከበረችኝ።


ከሁሉም ተርፌ እንደገና "ከሁሉም ለመትረፍ" አዛኑን ወደ አስተጋባው የአቅራቢያ መስጂድ እየተጣደፍኩ ገባሁ ። ጥድፊያየን ላየ የጀነት መግቢያዋን በ250 አለቀች ይላል በ250  እያለ የተጣራ እንጂ የተለመደው አዛን የተደረገ አይመስልም።

እውነት ግን ከአዛኑ ጋር የጀነቷን መግቢያ በ250 በ250 ይላል አለቀች አለቀች ቢባል ተጣድፈን እንገዛ ይሆን ? ወይስ እንደ አንዳንድ መዝለያ ፕሮግራም የለም የለም በአቅራቢያችን ባለ ባንክ እንድናገኝ እንድንገዛ ይመቻችልን እንል ይሆን?

ጫማዬን ለማውለቅ ዝቅ ብዬ ስመለከታት ምነው ምነው ሀበሽ? መርገጡንስ እርገጠኝ ተረገጥ ተብሎ የተፈጠረ  ወትሮስ ሌላ እጣ የለው: : አልረገጥም የለም አሻፈረኝ ቢልም እርግጫውን ቅጥ ያጣ ይሆንበት ይሆናል እንጂ ከመረገጥ አይዘልም:: በወግ መረገጥም እኮ ወግ ነው ::

ሀበሽ አረ ግድ የለህም አድምጠኝ  እኔም የምልህ ይሄንኑ ነው በወጉ እርገጠኝ መንገዱን ምረጥልኝ መንገድ ከመረጥክልኝ አለወግ ብትረግጠኝም እድሜዬ ይረዝማልና የመገላገል እጣ ይኖረኝ ይሆናል እንደው ከሰማዐኝ ልምከርህ ላንተም ስል ነው እንደው ምን አለ እያረፍክስ ቢሆን መርገጡ! ለአንተም እኮ ለጤናህ ጥሩ አይደለም እንደምታዬኝ እኔንም አቧራ ለአቧራ ስታኳትነኝ ሳሉ ቀትሎ ሊገድለኝ ነው ብላኝ ቀሰስ ያለች ትንታ ቢጤ ሳል ያሳለች መሰለኝ።

ተረጋጭ ሲመክርም ሲናገርም አይንህን ለአፈር ነውና ጫማ ማስቀመጫው ላይ ወዝፊያት ሽቅብ የመስጅዱን ደረጃ ወጣሁ እፎይ ያለች መሰለኝ ጫማዬ ለካ ለጥቂትም ጊዜ ማረፍ  ለጥቂትም መትረፍ እፎይ ያሰኛል።

ሰው የእለት ግዴታዬን ልወጣ ብሎ ወደሚገባበት መስጂድ እኔ ብሂሉን ቀይሬ የእለት ውዴታዬን ልወጣ ብዬ እየገባሁ ነበር ኡዱዕ ለማድረግ ሰልፍ ያዝኩ መቼም ለአዲስ አበቤ ሰልፍ እንደ አንገት ሀብል ጌጥ ከሆናት ቆየ ።


ሌላው ቢቀር ሰው እንዴት ለሽንት ቤት ይሰለፋል? አንድ አንድ ጊዜ ሰብር የሌለው አ*ም ባይ*ራስ ብሎ ተሰላፊውን አ*ም አመናጭቆ ይሄዳል ተሰላፊውም አ*ም ገርመም አድርጐት ፈገግ ይላል ፈገግታዋ መልዕክት አዘል ምፀት ናት።

ጓዴ ሲወጥርህ ትመለሳታለህን ከተሰላፊ አ*ም ወደ ትዕግስት የለሽ አ*ም ግልባጭ ለሽንት ቤቱ አስተዳደር የምትል መልዕክትን ታስተላልፋለች። አ*ም አ*ሙን እየገላመጠ ነው እኮ የማ*ራ የሚመስለው እንዲ*ራብን ቀበቶውን ተጋግዘን የምንፈታለት። ጐበዝ ከነአ*ችሁ ለምን አትከባበሩም በኋላ ያጣደፈው እንዳ*ራባችሁ ልል ዳዳኝና ድዴን ሲሉኝ ስለታየኝ ዝም አልኩ።

ሌላ ነገር ትኩረቴን ሳበው አንድ ሰው ላይ አይኔ አረፈ ኡዱዕ ለማድረግ ከተሰለፍን ከእኔና አንድ ከፊቴ ካለ ሌላ ሰው ውጪ ትጥበቱን የጀመረ አንድ ሰው ላይ አይኔ አረፈ።  እሰይ ተራዬ እስኪደርስ የማስበው አገኘሁ ይመስል ውስጤ ተፍነከነከ። በሁለት ነገሩ በሰውየው እኔና ውስጤ ተገረምን።

አንደኛ ለትጥበት (ኡዱዕ) ተብሎ የተዘጋጀ መቀመጫ እያለ አጐንብሶ መጠቀሙ እና ቧንቧዋን እንዳትሞት እነዳትሽር አድርጐ በጭላንጭል ከጭላንጭልም ጭላንጭል በሚመስል ከፍቶ ኡዱዕ እያደረገ መሆኑ ነው።

መቼም በዚሀ ቧንቧ አከፋፈቱ ኡዶውን ትቶ ባልዲ ቢደቅንበት ዘመን አልፎ ውሀው ሞልቶ  የምን መዝረክረክ ነው ብሎ
የሚዘጋው ደጃል ይመስለኛል ወይም ወይም በዚህ አደራረጉ የሚጨርስ ቂያማ ሲቆም ነው ያው የሞት መላይካውም ኡዶውን ከማቋርጠው ብሎ ትቶት ዘመኑ አልፎ የተነሱ መለከቱ ሲነፋ ኢቃም መስሎት ዞር ሲል ሰውዬ ቧንቧውን ዝጋውና እዚያ ሜዳ ላይ ሂድ ሂሳብ እየተወራረደ ነው ብሎ አንድ መላይካ ገላምጦት የሚሄድ ይመስለኛል።

ጥያቄዎች ውስጤን ወጠሩኝ ቆይ ሰውዬው ውሀ እያቆጠበ መስሎት ይሆን? መስሎት ነው እንበል ግን ቧንቧዋን በጥቂቷ ከፍቶ ውሀ ሲቆጥብ የራሱን ጨምሮ የብዙሀኑን ጊዜ በሰፊው ከፍቶ እያባከነው እንደሆነ አልተገለጠለትም ይሆን?

ስንቱ ይሆን አንዱን ቆጥቦ ሌላውን አብዝቶ ያባከነው?።የቆጡን አወርድ ብላ የሚባለውስ ይሄ ይሆን? ቆይ ከጊዜ እና ከውሀስ የቱን ነው መቆጠብ ያለብን? በውሀ ጊዜ ይሰራል? በጊዜ ውሀ እንጂ

የምንቆጥበው በውል ያልተገለጠልን የቆጣቢ አባካኝ የቁጥብ ብኩን የሆንን መስሎ ተሰማኝ።

ሰው ወይ አባካኝ ወይ ቆጣቢ ይሆናል ወይ አመዛዝኖ ይኖራል እንጂ እንዴት አንዱን ቧንቧ አፈንድቶ በአንዱ ቧንቧ ቀንሼ ልጠቀም ይባላል?

ጨርሶ ሲሄድ ምዕተ አለም አልፎ ቧንቧውን ለመዝጋት ደጃልን ያየሁ መስሎኝ ደንገጥ አልኩ ኢቃም ተባለ በሱም ደንገጥ አልኩ የተነሱ መለከት መስሎኝ ይሄ ሰውዬ አንድ ነገር ሳልከውን ትንሳዔዬን አመጣብኝ ብዬ።

የእሱን እለህ የተወጣሁ ይመስል ውሀውን አባክኜ ጊዜየን ቆጥቤ የመጀመሪያው መጐንበስ ላይ ደረስኩ እንደደረስኩ ልክ በማሽን እንደሚታጠፍ ወፈር ያለ ብረት አፍታ ሳይፈጅብኝ ከአጐንባሹ ጋር ተጐነበስኩ።


@Habeshistan