Get Mystery Box with random crypto!

በከፍተኛ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ መሆኑንም ባለሙያው ያነሳሉ፡፡ የብር ዋጋ ማነስ በውጪ ንግድ | Habesha online

በከፍተኛ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ መሆኑንም ባለሙያው ያነሳሉ፡፡
የብር ዋጋ ማነስ በውጪ ንግድ ገቢና በውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመነት ስበት ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ ቢኖረውም፣ ለውጭ ገበያ ከምትልከው በላይ የምታስገባው ከፍተኛ በሆነባት ኢትዮጵያ ጥቅሙ ያመዝናል ማለት እንደማይቻል የባንክ ባለሙያው ዳንኤል ይገልጻሉ፡፡ ዓለም ዐቀፍ የገንዘብ ተቋማት እንደሚመክሩት የውጪ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ አግዟል እንዳይባል፣ የብር ዋጋ በየጊዜው እየወረደ ባለበት ሁኔታ ኢትዮጵያ በከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ እጥረት እየተቸገረች መሆኑን የባንክ ባለሙያው ዳንኤል ይገልጻሉ፡፡
የገንዘብ ተመኑ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች የመግዣ ዋጋቸውን በመጨመር የገቢ ንግዷን ለመተካትም ቢታሰብ እንኳን፤ አገሪቱ በዋነኝነት ከውጭ የምታስገባው ነዳጅ፣ መድኃኒትና መሠረታዊ ሸቀጦች መሆናቸውን የሚገልጹት ዳንኤል፣ የእነዚህ እቃዎች ዋጋ መናር ከፍተኛ ቀውስ እንደሚያስከትልም ያስረዳሉ።
ዓለም ዐቀፍ የገንዘብ ተቋማት፣ አገራት የገንዘባቸው ዋጋ እንዲቀንሱ ከሚመክሩባቸው ምክንያቶች መካከል አንድ የውጪ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ ነው፡፡ ይሁን እንጂ፣ መንግሥት የብርን ዋጋ እንዲቀንስ በማድረጉ ኢትዮጵያ በውጪ ምንዛሬ እጥረት መፈተኗን ማስቀረት አለመቻሉን የባንክ ባለሙያው ዳንኤል ይገልጻሉ፡፡
የብር ዋጋ በየጊዜው እየወረደ መምጣቱ ጠቅላይ ሚኒስተሩ እንዳሉት ጥቅሙ የጎላ አለመሆኑን የሚገልጹት ዳንኤል፣ ለዋጋ ንረት ዋነኛ ምክንያት የሆነውን የብርን ዋጋ ማሳነስ አካሄድ ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ ችግሩ ካልተቀረፈ፣ ቢያንስ በብር ዋጋ ማነስ የሚከሰተውን የዋጋ ንረት ማስቀረት የተሻለ አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ በየወሩ የምታስመዘግበው የዋጋ ግሽበት ከ30 በመቶ በላይ በመሆኑ በዜጎች ላይ እያሳረፈ ያለው ኢኮኖሚያዊ ጫና ከፍተኛ ሆኗል። ከዋጋ ግሸበትም ጋር ተያይዞ መሠረታዊ የሚባሉ ሸቀጦች ዋጋ መናርም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ባለፉት ኹለት ዓመታት የተተገበረው የብርን አቅም ማሳነስ እርምጃ፣ መንግሥት እንዳሰበው ውጭ ንግድን ማበረታትና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን አለማስቀረቱን የባንክ ባለሙያው ይገልጻሉ፡፡ በየወሩ እየገሰገሰ ለሚገኘው የዋጋ ግሽበት መንግሥት የኢትዮጵያን ብር ዋጋ እንዲቀንስ ማድረጉ አንዱ ምክንያት መሆኑን ዳንኤል ይናገራሉ፡፡
መንግሥት የኢትዮጵያን ብር ካዳከመባቸው ምክንያቶች መካከል ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች ዋጋ ከረከሰ በርካታ ገቢ ይገኛል የሚል ነበር፡፡ እንዲሁም የወጪ ንግዱም ይበረታታል በሚል ቢሆንም ከምርታማነት እንዲሁም ከተወዳዳሪነት ጋር ተያይዞ በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
Source: Addis Maleda

@habeshaonlinebini