2021-08-29 13:59:23
ረድኤት
ክፍል 1
"የሴትነት አቅሙ እስከምን ድረስ ነው? ሴቶች ከወንዶች ይልቅ ጠንካራ ናቸው አላልከኝም?" ትላለች ለብቻዋ አልጋዋን በስስ እጆቿ እየደበደበች
"አልሸነፍም ነበር እኮ......እንዴት.. እንዴት" እንባዋ ከትዕዛዟ ውጪ ይሆናል ። ሳታስበው ታነባለች
ከአልጋዋ መተሻሸት ትራሷን ማቀፍ ከዛም ስለ ሽንፈቷ ማሰብ መቆጨት የዘወትር ተግባሯ ሆኗል
ረድኤት ነው ስሟ
አንድ ቀን ሀዋሳ ከጓደኞቼ ጋር እየተዝናናን ነበር ያገኘኃት ። ጓደኞቼ ውሀ ዳር መዝናናት ይወዳሉና እነሱ እስኪጨርሱ እኔ ዙሪያውን እየቃኘሁ ነበር
የዛኔ ነበር ረዱዬን ለብቻዋ ያገኘኃት ረዱዬ አልኩ እንዴ? ይቅርታ ረድኤት...
"ምነው ከጓደኞችህ ተለይተህ?" አለቺኝ
"ምነው ከቤተሰቦችሽ ተለይተሽ ?" ጥያቄዋን በጥያቄ መለስኩላት
እውነት ለማውራት አጠገቧ ልቀመጥ እንጂ እሷን የመተዋወቅ ሀሳቡም አልነበረኝም በቃ አለ አይደል ጓደኞቼ እስኪጨርሱ ከሰው ጋር ለመሆን...
"ውሀ ከመጠጥነት ባሻገር እንደዚህ ለመበጣጠስ መጠቀም አልወድም" አልኳት
ዝም
"ቦታውን እንዴት አገኘሺው?"
ዝም
ከረጅም ዝምታ በኃላ "ስለተፈጥሮ ልታስረዳኝ ትችላለህ?' አለቺኝ
ውስጤ መናገር እየፈለገ ዝም አልኳት (እሷ ዝም እንዳለቺኝ)
ትንሽ ቆይታ "እኮ የተፈጥሮ መልሱ ዝምታ ነው አንተ ጎበዝ ነህ አየህ ብዙዎቹ እናውቃለን እያሉ ተፈጥሮን በማይረባ የቃላት ጋጋታ ያውኳታል ፣ ጣዕሟን ያሳጡታል፣ ብልሆች ግን ዝምተኛዋን ተፈጥሮ በዝምታ ይገልጿታል።" አለቺኝ በግማሽ ግርምት
ደነገጥኩ !
ልጅቷ ያማታል? ወይስ ትፈላሰፋለች?
ረድኤት ተነስታ ሄደች
"ቤተሰቦችሽን አትጠብቂያቸውም?" አልኳት (እንድትቆይ ፈልጌያለሁ)
"ቤተሰቦቼ አይደሉም" አለቺኝ
ትንሽ አንደተራመደች "መሄድ ከፈለግክ ና.." አለቺኝ
ተከተልኳት
"ጓደኞችህን አትጠብቃቸውም?" አለቺኝ
"ጓደኞቼ አይደሉም" አልኳት
ሳቀች ..ደስ አለኝ
ከሩዱ ጋር ከተዋወቅን ሳምንት አስቆጠርን
ረዱ አንድ ቀን ታሪኳን እንዲህ ስትል አጫውታኛለች...
ቤት ውስጥ አራት ነን እኔ ትንሹ ወንድሜ ሄኖክ አባት እና እናቴ። በጣም የተሳካልን ቤተሰብ እንደሆንን ጓደኞቼ ይነግሩኛል። እኔ ገና ስኬት ማለት ምን እንደሆነ እንኳን በቅጡ አላውቅም ስኬት ማለት ለእነሱ ከብዙሀኑ የተለየ መሆን ማለት ነው። በዚህ ሚዛን ከታየ እኛ ቤት ከአብዛኛው የሀዋሳ ነዋሪ ህዝብ የተለየ ነገር አለ።ዘመናዊ አባት አለኝ። ዘመናዊ እናት እና ዘመናዊ ወንድም አሉኝ። የመጀመሪያ ልጃቸው ነኝ ሲበዛ ይወዱኛል። እያንዳንዱ ድርጊት እኔ ጋር ከመድረሱ በፊት እነሱ መንካት ወይም ማየት አለባቸው። አያምኑኝም የሁልጊዜ ምክራቸው ህይወታቸው እኔ እንደሆንኩ ነው። ይህ ነገር ምናልባት ብቸኛ ልጃቸው ስለሆንኩ መስሎኝ ነበረ ነገር ግን ትንሹ ሄኖክ ከመጣ በኃላም ይህ ጥንቃቄያቸው አልቀነሰም እንዲሁም በእጥፍ ጨመረ።
"አየህ ህይወትን እንዳውቃት አድል አልሰጡኝም! እኔ የማውቃት አለም እነሱ ያሳዩኝን ብቻ ነው። ያም ማለት ከአብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር አልተዋወቅም
በአንድ የታጠረ ግቢ ታጥሬ ነው ያለሁት ። የታሪክ መምህራችን የሰው ልጅ ነፃነት ያለው ፍጥረት ነው ሲል እስቃለሁ! ነፃነት በታጠረ ግቢ ውስጥ ከቤት ወደ ትምህርት ቤት መመላለስ ነው? ነፃነት አላደግሽም ተብሎ በእጀባ መንቀሳቀስ ነው?
ነፃነት አልኮረደድሽምና የኤርሚዬን አይን ማየት አትችዪም ማለት ነው?
"ኤርሚዬ ስትል ከተመሰጥኩበት ተመለስኩ፤ጓደኞቼን መካዴ ቆጨኝ"
"የት ሄድክ?" አለቺኝ
አለሁ እየሰማሁሽ ነው
ታሪኳን ቀጠለች.......
ይቀጥላል ሼር ላይክ
3.1K viewsGulilat Abebe, 10:59