Get Mystery Box with random crypto!

Grade 12 Results | 12ኛ ክፍል ዉጤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ grade12_results — Grade 12 Results | 12ኛ ክፍል ዉጤት G
የቴሌግራም ቻናል አርማ grade12_results — Grade 12 Results | 12ኛ ክፍል ዉጤት
የሰርጥ አድራሻ: @grade12_results
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.18K
የሰርጥ መግለጫ

#Welcome
‼️ የትምህርት ሚኒስቴር #ትክክለኛ መረጃዎች እዚ ይገኛሉ‼️
ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን።

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-03-10 08:15:11
#University of Gondar
    
  ጎንደር ዩኒቨርስቲ ለተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች እና አቅም ማሻሻያ ተማሪዎች  በሙሉ ወደ ግቢ መግቢያ ቀን መጋቢት11 እና 12  መሆኑን እሳውቋል፡

1.የአቅም ማሻሻያ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፋሲል ግቢ

2.የተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተማሪዎች ቴድሮስ ግቢ

3.የማህበራዊ ሳይንስ ሁሉም ማራኪ ግቢ የተመደባችሁ መሆኑን እንገልጻለን ሲል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ

https://t.me/grade12_results
360 viewsedited  05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 08:14:39
#DillaUniversity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል የትምህርት ፕሮግራም በተቋሙ ለተመደቡ ተማሪዎች በቅርቡ ጥሪ እንደሚያደርግ ግልጿል፡፡

ተቋሙ እያደረገ ያለውን ዝግጅት በቅርቡ እንዳጠናቀቀ በይፋ በመገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ የሚዲያ ገጾቹ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጽ www.du.edu.et ጥሪ የሚያደርግ መሆኑን አመልክቷል፡፡

ጥሪ እስከሚደረግ ድረስ በተቋሙ የተመደባችሁ ተማሪዎች በትዕግስት እንድትጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ
https://t.me/grade12_results
356 viewsedited  05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 19:22:55
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ PC ያስፈልጋቸዋል።

የተለያዩ አዳዲስ እና ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖችን በጥራትና በቅናሽ
ከ #ሄኒ_ኮምፒውተር ያገኛሉ።

ከአንድ አመት ዋስትና ጋር

ለተማሪዎች ልዩ ቅናሽ አለን።

የቴሌግራም ቻናላችን ላይ ዋጋቸውንና የላፕቶፖችን ዝርዝር መረጃ አስቀምጠናል።
ይመልከቱን
                
                 https://t.me/henicom
                 https://t.me/henicom
                
አድራሻ: አዲስአበባ፣ መገናኛ፣

: +251911903060
    
  Home of Laptops!
589 views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:35:37
ሐዋሳ ዩንቨርስቲ

በ2015 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ ሬመዲያል (Remedial Program) የተመደባችሁ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ የመግቢያ ጊዜ ከየካቲት 30-መጋቢት 01/ 2015 ዓ.ም መሆኑን ይገልጻል።

የምደባታ ቦታ፡-
በ Social Science የተመደባችሁ የስም ፊደል ከ A-L በቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩት ግቢ እንዲሁም የስም ፊደል ከM-Z በዋናው ግቢ

በ Natural Science የተመደባችሁ የስም ፊደል A-E በበንሳ ዳዬ ግቢ ፣ የስም ፊደል ከF-P በግብርና ኮሌጅ ግቢ እንዲሁም የስም ፊደል R-Z በዋናው ግቢ

የተመደባችሁ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቦታ በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰብያ ፡-
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ የሚከተሉትን ይዘው መምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡
1ኛ.  የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዋናውና ቅጂው
2ኛ.  ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክርቢ ዋናውና ቅጂው
3ኛ.  የሌሊት አልባሳት
4ኛ.  4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ
5ኛ. የስፖርት ትጥቅ
ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኃላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
     
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ  ሬጅስትራር እና አልሙኒ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ

https://t.me/grade12_results
1.1K views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:33:35
በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል (REMEDIAL) ተማሪዎች በሙሉ

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሪሜዲያል (REMEDIAL) የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ የካቲት 29-30/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ትምህርት የሚጀመረው መጋቢት 1/2015 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡

ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ የሚከተሉትን ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኃል፡፡

1ኛ. መሰናዶ ያጠናቀቃችሁበትን ሰርተፍኬት፣ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውን ከማይመለስ አንድ ኮፒ ጋር እና አራት 3×4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ።

2ኛ. አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የትራስ ጨርቅ ይዛችሁ መምጣት እንዳለባችሁ እናሳስባለን፡፡

3ኛ ይህንን የመግቢያ ጊዜ አሳልፎም ሆነ ቀድሞ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት


የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ

https://t.me/grade12_results
830 views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:32:17
" የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ አላስተናግድም " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ከትላንትና ምሽት ጀምሮ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ምደባ ይፋ አድርጎ ተማሪዎች የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ እየተመለከቱ ይገኛሉ።

በ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የተቋም ምደባቸውን 

- በWebsite: https://placement.ethernet.edu.et
- SMS: 9444 ላይ ነው እየተመለከቱ የሚገኙት።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ትምህርት ሚኒስቴር " የተቋም ይቀየርልኝ " ጥያቄ እንደማያስተናግድ አሳስቧል።

እንደትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ አጠቃላይ 106 ሺህ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠው የአቅም ማሻሻያ የትምህርት ፕሮግራም ላይ ተካተዋል፡፡

የአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) ፕሮግራሙ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውጪ ባሉ ሁሉም የመንግስት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል።

የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ
740 views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 21:31:54
Hp note book
Intel core i3
Generation- 10th
storage ፡ 256 Gb Ssd (10 times faster than normal hardisk)
RAM ፡ 8 gb ddr4 ram
Graphics ፡ intel hd graphics
Inch ፡14 inch infinity screen  ultra slim laptop
Battery -5 hours and above         Status: brand new with original charger and bag
፡ 29,500 birr


ይደውሉልን

location MEGENANGA

call Us@ +251911903060

IN BOX      @henok9030
        
Join our Telegram channel
       @henicom

.
805 views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 10:31:30
#ማስታወቂያ

የRemedial ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑንና በተመደባችሁበት የትምህርት ተቋሞች በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ  እንገልፃለን ።

ማሳሰቢያ :-
የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን።

የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች

Website:

https://placement.ethernet.edu.et
SMS: 9444

ትምህርት ሚኒስቴር
847 views07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 21:38:44
#ArbaMinchUniversity

በ2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የመግቢያ ቀን የካቲት 22/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ጊዜ ➧ የካቲት 23 እና 24/2015 ዓ.ም

ትምህርት የሚጀምረው ➧ የካቲት 27/2015 ዓ.ም

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧የ8ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣

➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና 2 ኮፒ፣

➧ የ10 እና 12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና 2 ኮፒ፣

➧ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ (4)፣

➧ የሌሊት አልባሳትና የስፖርት ትጥቅ።

የመመዝገቢያ ቦታ ➧የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ፤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በጫሞ ካምፓስ

ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጣ ተማሪን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ
887 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 18:19:23
#SPHMMC

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ በሕክምና የዲግሪ ፕሮግራም ለመማር ያመለከታችሁና የቅበላ መስፈርቶችን ያሟላችሁ የመግቢያ ፈተና እሁድ የካቲት 19/2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ ኮሌጁ አሳውቋል።

የመፈተኛ ቦታ ➧ መድኃኒአለም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት

ተፈታኞች የማንነት መለያ መታወቂያ፣ እስኪቢርቶ፣ እርሳስ፣ መቅረጫ እና ላጲስ መያዝ ይጠበቅባችኋል።


የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ

https://t.me/grade12_results
817 viewsedited  15:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ