Get Mystery Box with random crypto!

ጎዶልያስ ቲዩብ - Godoliyas Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ godolias_page — ጎዶልያስ ቲዩብ - Godoliyas Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ godolias_page — ጎዶልያስ ቲዩብ - Godoliyas Tube
የሰርጥ አድራሻ: @godolias_page
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.07K
የሰርጥ መግለጫ

የዩቲዩብ ቻናሌን ቤተሰብ እንሆን እናመሰግናለን
https://www.youtube.com/channel/UCJjmgy0CjHsjfIDNw6AZ2Zg

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-16 08:36:21
665 views05:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 08:28:01 የሰማችሁ ሸር አድርጉልን ላልሰሙት አሰሙልን ይህም ትልቅ በረከት ነው የአባቶች መልእክት
ከታች ያለውን ቪድዮ አድምጡት?
# ጀበራ ኪዳነምህረት በ1921 የተመሠረተች ሲሆን እንሰራለን ብለን ብንጀምርም በአሁኑ ስአት ከአቅማችን በላይ ሆነብን ።
የአካባቢው ህዝብ ከ3 አመት በላይ በድርቅ የተጎዳ
አንድ አመት በጦርነቱ ምክንያት በኢኮኖሚ የተጎዳን ሲሆን በአሁኑ ስአት ላምና በሪያችን ሽጠን ከዚህ ያደረስናትን ቤተክርስቲያን አሁን ለተከታታይ 3 አመታት በበጋው ፀይ በክረምት ዝናብ ሊያፈርስብን ነው?
ይህንን መረጃ ላልሰሙት ማሰማት በራሱ ትልቅ እርዳታ ነው እርዱን ብለዋል።

Account 1000323523979 Jebera k/ kiidane mihiret bete kiristian
እባካችሁ ስለ ኪዳነምህረት ብላችሁ እርዱን ብለዋል።

ለበለጠ መረጃ በ0905401198 ይደውሉ ?
672 views05:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 20:10:56
1.3K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 20:10:44 ለቅዱስነታቸው የተያዘው ጸሎት
በደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስነታቸውን መድኃኔዓለም ፈውሱን ሰጥቶ ወደ መንበራቸው በሰላም ይመልስልን።

በታሪካዊው የቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ያየሁት አርማ ነው የለጠፍኩት ትላንትና ለገዳማችን የሚያስፈልጉ ነገሮችን ለማየት በሄድኩበት ሰዓት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም ስገባ የተመለከትኩት ነው።

በሁለቱም የቤተ ክርስቲያኑ በሮች ከተዘረጋው ባንዲራና ቤተ ክርስቲያኑን ካሸበረቀው የባንዲራ ዲኮር ከፍ ብሎ የቤተ ክርስቲያን ርዕሰ መንበር የሆኑትን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ፎቶ በትላልቅ ባነሮች በሚያምር መልኩ ተዘጋጅቶ አየሁ።

በባነሩ ራስጌ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኩስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ይላል
በባነሩ ግርጌ
ከህመምዎ ድነው ወደ መንበረ ክብርዎ እንዲመለሱ ቤተ ክርስቲያን እና የመንፈስ ቅዱስ ልጆችዎ እንጸልያለን ይላል።
ደስ አለኝ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ለአባቶቻቸው ዋጋ ይከፍላሉ

ስመለከተው ቅዱስነታቸውን አሰብኳቸው አሁን በምን ዓይነት ሁኔታ አሉ ይሆን ከሄዱባት ቅጽበት ጀምሮ አሜሪካ ለህክምና ሄደው በሰላም እንደደረሱ ሰማን።

አሁን ያሉበት ነባራዊ ሁኔታ ግን ማንም የነገረን የለም ሚድያውና ዩቲበሮች የሆነውና ያልሆነውን ዘባርቀው ሐሳብ ውስጥ ከተቱን እንጂ አንዳችም አሁን ስላሉበት ደረጃ ሊነግሩን አልፈለጉም።

የE.O.T.c ሚድያ
የማህበረ ቅዱሳን ሚድያ
በጣም ይገርማል በየዕለቱ እየተከታተሉ ቅዱስነታቸው ያሉበትን ሁኔታ የት እየታከሙ እንደሆነ ሊነግሩን ይገባ ነበረ አልተነገረንም የቅዱስ ፓትርያርኩ ጉዳይ የመላው የኦርቶዶክሳውያን ጉዳይ ነው

በረከታቸው ይድረሰን ብፁዕ አቡነ አብርሃም
ጊዜ ሁኔታ ሰዓት ተመቻቸልኝ ያለው ሁሉ ባልተገባ መንገድ በቅዱስነታቸው ላይ ሲናገር በአጭር ጊዜ ከሀገረ ስብከታቸው በአስቸኳይ መጥተው የሚያሳርፍ መልስ በግላጭ ሰጥተው በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚነገሩ ያልተገቡ ንግግሮች ሁሉ በቤተ ክርስቲያን እንደ ተነገሩ እንቆጥራቸዋለን ስለዚ እያሰባችሁ ተናገሩ በይሆናል እየተናገራችሁ ቤተ ክርስቲያንን አትጉዷት ብለው የማያዳግም መልስ ስጥተዋል በረከታቸው ይድረሰን።

ሚድያዎች ባይናገሩም ባሉበት ሆነው በመንፈስ ይመለከቱናል እኛም ልጆቻቸው በጸሎት እያሰብናቸው ነው ብለው በውስጥ ያለውን የልጅነት ፍቅራቸውና በጸሎት እያሰቧቸው እንደሆነ የቅዱስ ዑራኤል ልጆች አስመስክረዋል።

ሌሎቻችንስ እያሰብናቸው ይሆን በእያንዳንዷ ጸሎታችን ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ርዕሰ መንበር ልንጸልይ ይገባል።

በርግጥ በቤተ ክርስቲያናችን ጸልዩ በእንተ ርእሰ ሊቀ ጳጳሳት አቡነ ማትያስ ትላለች አሁን ደግሞ በተለየ መንገድ ሁላችንም በጾማችን በጸሎታችን ልናሳስባቸው ይገባል።

የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ወጣቶችና ሰንበት ትምህርት ቤትን ግን ሳላመሰግን አላልፍም አርአያነታችሁን ገልጣችኋልና እናመሰግናለን።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ሚድያዎች አሁንም ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ እንድትገልፁልን እንፈልጋለን።

የቅዱስነታቸው በረከት አይለየን በሰላም በጤና ይመለሱልን

ጸልዩ በእንተ ርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት አቡነ ማትያስ ወበእንተ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ወበእንተ ብፁዕ አቡነ ዮናስ ወበእንተ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

ስለ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ስለ አባ ማትያስ
ስለ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ
ስለ ብፁዕ አቡነ ዮናስ
ስለ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ ጸልዩ

ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
ስለ ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
ስለ ሚራቡ ስለ ሚጨነቁ እንጸልይ
ስለ ታመሙት በየ ሆስፒታሉ በየጸበሉ በመከራ በጭንቅ ስላሉት እንጸልይ
ያለበደላቸው ያለ ኃጢአታቸው ደማቸው አየፈሰሰ ስላሉ ንፁሃን እንጸልይ አምላከ ሰላም ሰላሙን ይስጠን

አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
አዲስ አበባ 26/11/2014
1.2K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 03:14:36
1.0K views00:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 03:14:00 ወጣት ሳምራዊት ደስታ እንታደጋት በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵይዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዴሁም በአገር ውስጥ የምትገኝ ለሳምሪ የህክምና ወጪዋን ለመሸፈን በተከፈተ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አቅም ያለው በገንዘብ አቅም የሌለው በሜችለው በፀሎትም ሼር በማድረግም ለልጆ ለህልሞ ስንል እንታደጋት እንርዳት::

ዘወትር ለበጎ ነገር የማትታክቱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ የአቅማችሁን እንድታደርጉ በእግዚአብሔር ስም እንማፀናለን።

ንግድ ባንክ
Commercial Bank of Ethiopia (CBE)
1000180776145 ገነት ጀምበሩ ዳምጠው (እናቷ)
ለተጨማሪ መረጃ +251 91 038 4728 / +251 91 337 9447
957 views00:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 21:00:13
1.8K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 20:59:49 «መልካም ወጣት¡ »

ዝ ውእቱ ትሩፋተ መልካም ወጣት #ዘፓስተር #ዮናታን ፕሮቴስታንታዊ በውስተ ትእይንተ ሐዋሳ!

ከዚህ የመናፍስት አሰራር የሰወረህና የሰወረሽ ማን ይመስገን?

ተዋህዶ ርትዕት፣ ስንዱ እመቤት፣ የእረፍታችን ቦታ፣ ኩራታችን፣ ሰላማችን፣ ፀጥታችን ሆይ ክብር ይገባሻል! መርጦ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ያደረገን የቤተክርስቲያን እራስ፣ የድንግል ልጅ መድኀን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ከአፅናፍ ዓለም እስከ አፅናፈ ዓለም የተባረከና የተመሰገነ ይሁን አሜን! የመንፈሳችን ሰላም የማዕዘን ድንጋይ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንወድሀለን፣ እናመሰግንሃለን፣ እናመልክሀለን!

እንግዲህ መልካም ወጣት በሚል መንግስታዊ የፕሮቴስታን እምነት ማስፋፊያ ፕሮግራም ላይ የሚሳተፉ አዕምሯቸው የነፈዘ፣ በአጋንንት አሰራር እረፍት ያጣ ወጣቶች ይሆን ይመስላሉ!

More than 90% of youth's in this religion are said to have mental deviation and psychiatric component! Due to false prophets and preachers the young generation is being transferred to the bad spirit world!

ስለዚህ ከዚህ የመናፍስት አሰራር የሰወረህና የሰወረሽ ማን ይመስገን? ድምፃችሁ አይሰማም!!! ማን ይመስገን????

# እልል በሉ

እልል በሉ በአንድነት ዘምሩ
አመስግኑ ለክብሩም ዘምሩለት
እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም በሉ

አዝ--------

በኃጢያት ባርነት ስንኖር ተገዝተን
ከቤቱ ስንርቅ ትእዛዙን አፍርሰን
አይቶ ዝም ያላለን ጠላቶቹ ሳለን
ውለታው ብዙ ነው ክብር ለዕርሱ ይሁን/2/

አዝ-------

ራሱን አዋርዶ እኛን አከበረን
ሥጋውና ደሙን ብሉ ጠጡ አለን
መልካም እረኛ ነው የሚያሳጣን የለም
ምስጋና ይድረሰው ለመድኃኒአለም/2/

አዝ------

ሕይወቱን የሰዋ እንደ አምላክ ማን አለ
ለሰው ልች ብሎ በመስቀል የዋለ
ፍቅሩ አይለካ አያልቅም ቢወራ
ከሰማያትወርዶ ሆነ ከእኛ ጋራ/2/

አዝ-------

ሥራውን እናድንቅ እንዲህ ለወደደን
ከማያልቀው ፍቅሩ በረከት ላደለን
ለማይነገረው ለአምላክ ስጦታ
ውዳሴን እናቅርብ እንዘምር በእልልታ/2/
1.6K views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 17:28:33
1.8K views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 07:28:34
2.7K views04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ