Get Mystery Box with random crypto!

ግጥም እና ጥበብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ getami_mintesnot — ግጥም እና ጥበብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ getami_mintesnot — ግጥም እና ጥበብ
የሰርጥ አድራሻ: @getami_mintesnot
ምድቦች: ጥቅሶች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.60K
የሰርጥ መግለጫ

የግጥም መፀሐፎች
የግጥም ድምፆች
አንዲሁም የተለያዩ የጥበብ ወጥቶች ምቀርብበት
ኑ ይቀላቀሉን☺☺☺
እባካቹን ተቀላቀሉን

✋አንዴ🤚
አስተያየት ካላቹ
👇👇👇👇👇👇👇👇
Contact me @Mintesnot_suleyman

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 07:25:05 (የሆነውን ላለውጠው
ለእንባዬማ ፊት አልሰጠው።
በዕዉቀቱ ስዩም)
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨


አላነባም ለቀን
አላለቅስ ለጊዜ
ያለፈ እንደው አልፏል
መጪው ነው ደሞዜ

መንገድ አዙሪት ነው
ሄደችብኝ ብዬ መንገዷን አልከሰው
ተራርቆ አይቀረም
ሁሌም ይገናኛል ሞቶ ካልቀረ ሰው
እንገናኛለን ምን መንገድ ቢለየን
ተራራቅን እንጂ መቼ ተለያየን።

ዮኒ""
94 views🅢🅞🅛🅐 ༒ًٍٜ۪۪۪۪۪ٜٜٜٜٖٜٜٜٖٜٖ͜͡YNWA, 04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 18:35:19 ከግጥሞቼ
=======
ከግራህ
++++

እኔ
መሆንን እንድሆን
አንተን እያየዉኝ
ባይንህ ስርጉዶች ዉስጥ
እራሴን ፈለኩኝ
ፈለኳት
ምትሻትን እንስት
እሷኑ መስዬ
አንተን እንዳስደስት
አብሬ እየተጓዝኩ
ምትርህን ቃኛለዉ
የቷ ትስብ ብዬ ከብሌንህ እረፍት
አብሬ አርፋለዉ
ድንገት እኔነቴ
አንሶብህ እንዳልገኝ
ፍርሀት ቢዉጠኝ
ያቺኛዋን ወጣት
ምናብህ የሳላትን
ለመሆን ስጣጣር
ብሆን ማስመሰልን
ደሞ ተቀይረ
ሌላኛዋን ብትሻስ?
እሷን መሆን
ቢያቅትስ?
እላለዉ
እብሰለሰላለዉ
ከጎንህ መሆኔ
ከአይንህ ቢሰወርም
የሆንኩትን ስሆን
ከፊትህ አልመጣዉም
አይን ክፉ
መመኘት ነዉ ላየዉ ሁሉ
ስንቷን እንስት
በምኞት ቤት አዋልክ አሉ
እኔም ትቼ መሆንን
ሆኜ ባለሁበት ቆየዉ
ሴትነቴን ከአይንህ ሳይሆን
ከጎንህ ላገኘዉ
በግራህ ጎን ተወሽቄ
ስሪቴን ልመልከት
ያርግልኝ ግጣሜን
በዛዉ እንድከተት
ምትሻትን ሳይሆን
ምታሻህን እንስት
ሄዋንህ ነኝና
ባንተ ምትደሰት
ልዋል ልደር
ልቆይ በዚያ
ስትነቃ እንድታየኝ
አዳም'ኤ በጉያ።

ተፃፈ በሰላም
share and join us

@learneachother
For any comment

@selamnen
295 viewsSelam Bishaw, 15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 21:26:00
ክፉ ነህ ይሉሀል ማስረጃ አስቀምጠዉ
ሰይጣንም ብለዋል አጥንትህን ረግጠዉ
እኔ ግን እላለዉ
ቀድሞም ሰይጣን ቢሆን መላክ ስለነበር
መልክህን ያሳያል የአባይ መጠንከር።

እዉነታዉን መካድ አይቻልም።
@learneachother
ተፃፈ በሰላም
501 viewsSelam Bishaw, 18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 14:49:13 ዋ! ሰብዕ

ይኸውልህ አለሜ
እኔ ያንተው ገፊ
ከትናንት አንደበት
ከዛሬው ልሳኔ ከነገ ቃል ዋጀሁ
ይሆል እያልኩኝ
በይሆናል ተስፋ ስንት ዘመን ፈጀሁ።
ሰባት ሀሳብ ይዞ
ራስን የሚያህል
ድብቅ ወርቅ ግልጥ ሰም
ዝተታም ማፍቀርህ
ከነጣው ልቤ ላይ እንደምን ምን ይክሰም?!
መክሰሙስ ባልከፋ…
ብን እብስ ይበለው
እስከአመዳም መልኩ
ወትሮስ ፍቅር ተባይ
እሳት አይደል ልኩ?!
ይኸውልህ ዛሬም…
ከሰባቴ ሰባት
አንድ አላገኝ ብዬ ስባዝን ስባዝን
ቀን ሄዶ ቀን ጠባ በሀዘኔ ሳዝን።
አሁንማ…
ተለማመድኩ መሰል
ከሳቀው ሳቅ መዋስ
መፍጠር አዲስ ህዋስ
ያልፋልን እላለሁ
ተስፋ አነጋለሁ ተስፋ አመሻለሁ
እኔ ያንተው አፍቃሪ
መቼ እሸሻለሁ?¡
ግን አንድ እድፍ አለኝ
ከሁሉም ከሁሉም ገዝፎ የሚታየኝ
ነጥሮ ሚጎላብኝ
ግን…ደሞ
የወደደ ሁሉ መሳ አይወደድም
ቆብ ከዐይን ቢተኛም
እንቅልፍ ሳይረገዝ
ህልም አይወለድም(…አይደል)
ያኔ…ድሮ
በኮልታፋ አንደበት
ሀ-ግዕዝ ሁ-ካዕብ…
እለፍፈው ነበር ፊደል እያዳፋው
አሁን ዛሬ
በተሳለ ምላስ
ዋ-ሰብዕ እላለሁ
ምንስ ፊደል መናገር ለጠፋው?!

[ረድኤት ሰኢድ መሀመድ]



@seyamuhe
@seyamuhe
902 viewsረዱ, 11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 22:40:01 ከግጥሞቼ

እዬዬ ቢበዛም ደረት ብንደልቅም
ገዳይ ካልበቃለት ከመሞት አንድንም።

ተፃፈ በሰላም
@learneachother
@selamnen
870 viewsSelam Bishaw, 19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 22:12:24 ከግጥሞቼ

ዛሬ ወይስ ትላንት
==========
ብረገጥ ይበጀኝ ቢበዘበዝ ሀብቴ ቢመታ ገላዬ
እየበለፀኩኝ ከምትበን ነፍሴ ከሚፈስ እምባዬ።

ተፃፈ በሰላም
share and join us

@learneachother
@selamnen
159 viewsSelam Bishaw, 19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 22:20:34 1 ነን
====

ዘመናት ያበጀን ቀናት ያደራጀን
በልዮነት አድማስ ፍቅር ያጣመረን
እንደ ችቦ መብራት ብርሀን የፈጠርን
ህብረ ብሔርነት ቀለሙን ያተምን
እኛ አንድ ነን።
ድንጋይን ፈልፍለን ህንፃ የገነባን
በራሳችን ዘይቤ ፊደላት የሰራን
የዜማን መዋቅር ቀድመን የዘመርን
የሰዉ ልጅ መገኛ ድንቅ ተፈጥሮ ያለን
እኛ አንድ ነን።
የጊዜዉ ሁካታ ከቶ የማይረታን
የነካኩን ጊዜ ማንም የማይገታን
አሻፈረን ላልን ወኔያችን ማይላላ
በወንጨፎ ጠጠር አንገት የምንቀላ
የተባበርን ለ'ት አለም የሚፈራን
መጀገን የቻልን ከጀግኖች የተማርን
አባይን ገድበን ገድልን የገደልን
እምቢ ለጠላቴ ብለን የሸለልን
እኛ አንድ ነን።
እናም ዛሬ
የጓዳችን ኩርፊያ ጠበኛ አያድርገን
ከወንድም ቤተሰብ አያቀያይመን
መነቋቆር ትተን
ልዩነትን ጥለን
እንደጥንቱ እንስራ
ለሀገር እናብራ
የበደለን ምረን
ነገን ተስፋ አድርገን
ሀሰትን ተቃዉመን
ለእዉነት ደግፈን
ኢትዮጵያዊነትን በጉልህ እንፃፈዉ
ከቶ እንዳይደበዝዝ የኛን እንጣለዉ
እጆች ተዘርግተዉ ወደፈጣሪያችን
ድምፃችን ተሰምቶ የፀሎቶቻችን
ማረሻ አድርጎልን ሰይፍና ቢላን
ድንቁርናዉ ጠፍቶ እንሁን ሰላምን
እኛ
በነጠላ አንደበት ለስም የማንበቃ
ለየለብቻችን ጤፍ እንኳ ማንወቃ
አብሮነት ያሰረን
አምላክ የፈተለን
ከጊዮን ጠጥተን ከምድሯ የጠገብን
እንኳንስ ለዘመድ ለባዳ የተረፍን
አንጀት የሚበላዉ አነጋገራችን
የትም ማይገኘዉ ወጉ ባህላችን
አንድነትን አልፈን አንዱን ራሱን የሆን
ኢትዮጲያዊ ብቻ ሳንሆን ኢትዮጵያ ነን።
1 ነን!!!

Share and join us

@learneachother
@selamnen
280 viewsSelam Bishaw, 19:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 18:57:40 ለበላይ

ከህብረ-ቃል መዞ ወርቁን የሚለየዉ
የለየዉን እዉነት በገሀድ ሚገልጠዉ
አሻፈረኝ ማይል ወቅሶ ለመገሰፅ
ዉሸትን ተቃርኖ ለእዉነት የሚያምፅ
ሺ'ዉ ስለተንጫጫ የማይነቃነቅ
ላመነበት ጉዳይ ራሱን የሚያሳንቅ
ወገንተኛ ያልሆነ የሰዉ ሁሉ አንደበት
የ'በላይ ነዉ ስሙ ግብሩ ለነፃነት
በ'በላይ
ጭቆና ተወግዞ
ሀቃችን ተመዞ
ከፊደላት በላይ የነርሱን ቤት መቷል
ከማስጨብጨብ ዘሎ ከልባችን ገብቷል

የህዝብ ድምፅ ማጥፋት
የጥበብ ቤት መዝጋት
ይበልጥ ያነሳ እንጂ ብዙ የህዝን ድምፅ
ይበልጥ ይፈጥር እንጂ ጥበብን የሚቀርፅ
በነካኩን ቁጥር ሲጭሩን ምንበዛ
ባንዱ የበላይ ምክንያት እልፍ የበላይ ገዛ
ለራሱ አበዛ
አንተ ጀግናዉ በላይ ብትሞትም አይቆጭህ
ለሰዉ አምላኪ ሰዉ እዉነቱን መንገርህ
ልክ ነበር ብለን እንድንል አርጎናል
ቀረ ያለነዉ እፈና ዛሬ ይፋ ሆኗል
የበላይ ልጅ ነበርክ ያዉም የኢትዮጵያ
የፊደላቶች ሀቅ የእዉነት ማሳያ!

#በላይ በቀለ ወያ የት ነዉ?!
እኔም ለርሱ ድምፅ ነኝ!!

ተፃፈ በሰላም

share and join us

@learneachother
@selamnen
307 viewsSelam Bishaw, 15:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 19:05:38 አለህ!

ከመቀመጥ መነሳቱን
ከመጠንከር መሳሳቱን
ከሆንኩበት እንዳልገኝ
ስውር ጥፍት የሚያደርገኝ
አለህ አስማት አለህ አዚም!

እንጃ ብቻ እንጃ እንጃ
የአንተን አስማት የ'ኔን ፍርጃ
ከደቆሰኝ የእብሪት ስሜት
ከልገኝም ባይነቴ
ካንተነትህ ስፍር ቀለም
ሲጠለስም እኔነቴ
ምን ይባላል አሁን ይሄ
አስማት ብሎ ከመሰየም?

ከንጣትህ የ'ኔ ፅልመት
ከብርታትህ የ'ኔ ድክመት
ቅይጥ ሆኖ ቢያብረቀርቅ
ቅኔ ቢሆንም
አጣሁለት ሰምናወርቅ
ልኬ ፈርሶ ልክ አጥቼ
ልክ ላገኝ ልኬን ሳጣ
ፈቅታዬን ከአካልህ ሳሳርፈው
ወዛም ፊቴ ከገረጣ
ከሄድኩበት የጉዞ ዕትም
እግሬ ቢገኝ ከእግርህ የትም
ምን ይባላል አሁን ይሄ
አዚም ብሎ ከመሰየም?

ምድረ ወንድ አዳም ተባይ ስፍሩ ሰው
ህቡዕ ሆኖ
ጣዕም ጠረኑን ያልቀመሰው
የ'ኔን ጣራ የዕድፌን ዳር
ማን ሸለመህ
ከልቤ ጋርውሎን ማደር?
አንተ ሆዬ በየት በኩል
የጠራረክ የነፍሴን ኩል
ጋን ኩራቴን
በንኬሉ ጨልፈህ የደፋህ
ለመሆኑ ማን ነኝ ባይነህ
ጨረር ገፄን ደርሰህ ያጠፋህ?

ቢኖር እንጂ×፪
አንድ መንፈስ የሆነ አካል
ብኩን ህልሜ
በእንቅልፍህ መች ይለካል
ከሸበተ ነጭ ካወጣ ከልቤ ቅል
ፍቅር የሚሉት ለጋ ነገር ቢበቃቅል
ግርም አለኝ ግ ር ም!
ለነገሩ……እንዴት አይደንቅ አያነቃን
ልብስ ጌጡ ለገላ ዕርቃን¡

[ረድኤት ሰኢድ መሀመድ]
328 viewsረዱ, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 22:47:41
አንቺ ኢትዮጵያ የደም ጣና
የሰቆቃ መንደር የእንባ ጎዳና
የልጆችሽን ሬሳ እያየው በመንገድ
ከንፈር ብመጥልሽ ምንም አልፈይድ
እንደው
መንግስት የለምና ለእውነት ሚጠራ
እንደ አቤል ደም የላይኛውን እንደተጣራ
ለቅሶሽ ጎኑን ትቶ ወደ አሪያም ያምራ
ምናልባት ፈጣሪ ሰምቶሽ ከራራ

Sola
342 views🅢🅞🅛🅐 ༒ًٍٜ۪۪۪۪۪ٜٜٜٜٖٜٜٜٖٜٖ͜͡YNWA, 19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ