Get Mystery Box with random crypto!

እጅ ከፍንጅ የተያዘው ትህነግ /ህወሓት ትህነግ በማያወላዳ መልኩ በአማራ ላይ የጦርነት ውሳኔ መወ | Getachew shiferaw

እጅ ከፍንጅ የተያዘው ትህነግ /ህወሓት

ትህነግ በማያወላዳ መልኩ በአማራ ላይ የጦርነት ውሳኔ መወሰኑን ሳይደባብቅ የካቢኔ ውሳኔውን በመግለጫ አሳውቋል። ይህ መግለጫ የተሰጠበት ዋናው ምክንያት ትህነግ የጦርነት ዝግጅት ሲያደርግ እጅ ከፍንጅ ስለተያዘ፣ ለዚህም ወንጀሉ ማቅለያ ይሆነኛል የሚል አማራ ላይ ብቻ እንደሚዘምት ለማሳወቅ ነው!

1) አብይ አህመድ የጓዳ ስምምነቱ አላዋጣው ሲል የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ አንድ ወር ውስጥ ትጥቅ መፍታት የነበረበትን የትህነግ ታጣቂ አሁን ትጥቅ ለማስፈታት ሽር ጉድ ይዟል። ትህነግ ደግሞ ላለመፍታት ብቻ ሳይሆን ለጦርነት እየተዘጋጀ ነው። ትህነግ ትጥቅ ላለመፍፋት ራቅ አድርጎ የዘጋጀበትን ጦርነት በቅርብ ለማድረግ ጥድፊያ ላይ ነው። አብይ ይህን የትህነግ ዝግጅት ሰሞኑን በቲቪ ከመናገሩ በፊት ለአደራዳሪዎቹም፣ መቀሌ ደርሰው ተመልሰው ለሚጨቀጭቁት አምባሳደሮችና ሌሎች አካላትም በተለያየ መልኩ ካደረሰ ቆይቷል። አደራዳሪዎቹን ጨምሮ ሌሎች አካላትም የጦርነት ዝግጅቱ እንዳለ አሳምረው ያውቃሉ። ትህነግም በቅርብ ጦርነት ልትጀምር ነው ተብሎ በዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በመረጃ ተነግሮታል።

2) በቅርብ ዘፀአት በሚል አካውንት የሚፅፍ የትህነግ ደጋፊ ትህነግ በውጭ አገርና በአገር ቤት ኮሚቴ አዋቅሮ ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑን ፅፏል። የትህነግ አባላት ቃል በቃል "ጦርነት አንፈልግም" እያሉ የሚፅፉት ዝግጅቱን ስለሚያውቁ ነው። የአንድ የትግራይ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ከአሜሪካ ተወካዮች ጋር ስብሰባ አድርገው ሲወጡ "እኛ ጦርነት እንደማንፈልግ፣ ህወሓት ለጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑን ነግረናቸዋል" ብሎ ፅፏል።

4) ስለ ትህነግ የጦርነት ዝግጅት በርካታ ጉዳዮችን ማንሳት ይቻላል። በአውሮፕላን በሌሊት መሳሪያ እንደገባለት ሲነገር ጫጫታ የተፈጠረው ሀቁ በመታወቁ ነው። ትህነግ ለጦርነት እየተዘጋጀ እንደሆነ እየቀረበበት ያለው ክስን ማስተባበል የማይችልበት በመሆኑና እጅ ከፍንጅ የተያዘበት በመሆኑ ሌላ ማቅለያ የመሰለውን መረጃ ማስተላለፍ ፈልጓል። እጅ ከፍንጅ የተያዘበትን ጦርነት ከአማራ ጋር ነው የማደርገው ብሎ በጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ያለ ማቅማማት ገልፆታል። ለዚህም እጅ ከፍንጅ የተያዘበትን የጦርነት ዝግጅት ውንጀላ ያቀልልኛል ያለባቸው ምክንያቶች አሉት።

5) ትህነግ ጦርነቱን ከአማራ ጋር አደርገዋለሁ በሚል የማይረባ ሰበብ ይዞ የመጣበት ምክንያት አለው። አደራዳሪዎቹን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የጦርነት ዝግጅቱን በመረጃ ስለደረሱበት የሰላም ስምምነቱ ተጥሶ ነው የጀመርኩት ማለት ይፈልጋል። ታጣቂውን እንዲያስፈታ ገንዘብ ቃል እየገቡ ላሉት ጨምሮ ለሌሎቹም ትጥቅ የማይፈታበትን ሰበብ ከአሁኑ አቅርቧል። ከፊቴ የጦርነት ድግስ አለኝ ብሎ የጦርነት እቅዱን አሳውቋቸዋል። ለኦሮሞ ብልፅግና፣ ለኤርትራና ለሌሎች ኃይሎች ደግሞ ከአማራ ጋር ነው ጠቤ ብሎ መነጠሉ ነው። ጦርነቱ የአማራ ብልፅግና ጋርም አይሆንም። ሸሽቶ አዲስ አበባ ያለውን ካድሬ ሳይሆን የራያና ዋግ፣ ወልቃይትና ጠለምት ንፁሃንን እንደሚወር ግልፅ ነው።

6) የትህነግ የጦርነት ሰበብ እጅ ከፍንጅ የተያዘበትን ከማስቀየር ውጭ ምክንያት ያለው አይደለም። አካባቢዎቹ አወዛጋቢ በተባሉበት ሁኔታ ራሱም በትምህርት ብቻ ሳይሆን በየቀኑ በተለያየ መንገድ በሀሰት "የትግራይ ናቸው" እያለ ቀጥሏል። ከአሁን ቀደም ራስ ዳሸንና ላሊበላን የትግራይ አካል አድርጎ በትግራይ መማሪያ መፅሐፎች ያሳተመው፣ በዚህ ወቅት የምንዋሰነው ከአገውና ቅማንት እንጅ አማራ የሚባል ህዝብ የለም እያለ በየመድረኩ ያለ ሀፍረት የሚሰብከው፣ አማራን የሚሳደብ ሙዚቃ አሁንም ስፖንሰር እያደረገ የሚያሳትመው፣ ጠላቴ አማራ ነው ከሚለው ማንፌስቶው በስራም በአስተሳሰብም አንድ ክንድ ያልራቀው እንዲያውም ከድሮው ማንፌስቶ በባሰ እየሰራበት ያለው ትህነግ ነው ሰበብ ፈጥሮ ጦርነት ያወጀው።

7) ጦርነቱ በጊዜያዊ አስተዳደሩ በኩል የነገረበት ምክንያትም አለ። አብይና ደጋፊዎቹ የጌታቸው ረዳን ቡድን ጦርነት የማይፈልግ አስመስለው እያቀረቡ ነው። ራሳቸው ተመልሰው ግን ጌታቸው ረዳን ከግብፅ ጋር እየተገናኘ እንደሆነ እያስነገሩ ነው። ከኤርትራ ጋር መገናኘቱ ይታወቃል። ትህነግም እጅ ከፍንጅ የያዘው በጋራ ዝግጅት መሆኑን የተናገረው በእነ ጌታቸው ረዳ በኩል ነው። ይህ የሆነው ለጠላትም ለወዳጅም ወደ ጦርነቱ በአንድነት እንደሚገቡ ማሳወቅ ስላለባቸው ያደረጉት ነው።

8/ ትህነግ በሰላም ስምምነቱ ሲያወናብድ ከርሟል። ትጥቅ ሳይፈታ "የሰላም ስምምነቱ ይከበር" ሲል ከርሟል። የደቡብ አፍሪካው ስምምነት ላይ አወዛጋቢ የተባሉት ወደ ትግራይ ይካለሉ ባላለበት "በስምምነቱ መሰረት ይመለሱልኝ" እያለ ሲያጭበረብር፣ በአማራ ክልል ካድሬ ጅልነት ያለ ስምምኑ ስምምነት ይከበር ሲል ከርሟል። በቅርብ ነገሮች አፍጥጠው መጡ። ተደራዳሪ የነበሩ "ግዛቶቹ በአማራ ክልል ይቆዩ ነው የተባሉ" ማለት ሲጀምሩ መልስ አጣ። አብይ ለራሱ ስጋት ሲባል ትጥቅ ለማስፈታት ሲፈልግ እነ ደብረፅዮን "የሰላም ስምምነቱ ከእኛ ፍላጎት ውጭ በጥቂት ሰዎች ስህተት የተፈረመ የማናውቀው ውል ነው" ብለው ካዱት። በቅርብ በተደረገው የአደራዳሪዎቹ ግምገማ እነ ደብረፅዮን ሌላ ስምምነት ብቻ ሳይሆን አዲስ አደራዳሪ እንደሚፈልጉ የትህነግ/ህወሓት ጉምቱ ባለስልጣን ልጅ እና የጌታቸው ረዳ ቡድን አክቲቪስት ፅፎት አጀንዳ ሆኖ ነበር። አሁን ትህነግ እያወናበደ የትም እንደማይደርስ ተረድቷል። ትጥቅ ፍታ ተብሎ ዶላር ተሰብስቧል። በትግራይ ብዙ ታማኝነቱን ያጣው ትህነግ ታጣቂዬን አጥቸ ማንም እንደፈለኩ ያደርገኛል ብሎ ሲያወናብድበት የከረመውን ስምምነቱ በጦርነት አዋጅ አፍርሸዋለሁ ብሎ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በኩል በይፋ አሳውቋል። የጦርነቱ አዋጅ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በተቋቋመው አካል የተነገረ ነው።

9) ምን አልባት ትህነግ ይህን የጦርነት አዋጁን እንደ ማመልከቻም የሚጠቀምበት እድል ይኖረዋል። የደቡብ አፍሪካውን ስምምነት አላውቀውም ብሎ የጦርነት አዋጅ አውጇል። ጦርነቱን ጀምሮም ጦርነቱ ያሳሰበው ዓለም አቀፍ አካል ወይም የደቡብ አፍሪካው አደራዳሪዎች "ተው" ካሉት በአዲስ አደራዳሪ ሌላ ጊዜ መግዧ ስምምነት ሊጠይቅ ይችላል።

አንዳንዶች የትህነግ የጦርነት ቅስቀሳ አካል ሆነው የትህነግን የጦርነት አዋጅ ማስጠንቀቂያ አስመስለው እያለማመዱን ነው። አንድ ክልል በካቢኔ ደረጃ በሌላው ላይ መሰል ውሳኔ እንዲያስላልፍ መብት የለውም። እውነት ቢሆን ኖር ትህነግም ለአደራዳሪዎቹም ለፌደራሉ ብልፅግግናም ሊያቀርበው የሚትለውን አቤቱታ ነው የጦርነት ፊሽካ አካል ያደረገው።

ጦርነቱን ከአማራ ብልፅግና ጋር የሚያስመስሉም የጦርነት ዝግጅቱ አካላት ወይንም ራሳቸውን የሚያታልሉ ናቸው። አማራ ብልፅግና የአማራን ህዝብ የማንነትም ሆነ የግዛት አንድነት ቀርቶ ሌላ ቀለል ያለ ጥያቄ መፍታት የማይችል ኃይል ነው። የአማራ ብልፅግና ከትህነግ ጋር መሰል ውዝግብ ውስጥ የገባ የሚያስመስሉ አካላት ብልፅግና ለአማራ ህዝብ የቆመ አስመስለው ሊያሞኙን የማፈልጉ ናቸው። የትህነግ የጦርነቱ አዋጁ ግልፅና ህዝብ ላይ ነው!

የጦርነት አዋጁ ማስተባበል የማይቻለው የጦርነት ዝግጅትን፣ ቀጣዩን ጦርነት ማለማመጃ ተደርጎ አሳውቀን እንግባበት ተብሎ በሰላም ስምምነቱ በተመሰረተው ጊዜያዊ አስተዳደር በሌሎች ጉዳዮች ሲጣስ የከረመው የሰላም ስምምነቱ በጦርነት አዋጅ የተጣሰበት ነው።