2022-07-04 18:18:12
የገደል ...ማ...ሚ...ቱ
የትናትናንትና ሰወች የሉም ከሰሙ...አምጠው የሠጡን ክፋት እንጂ...የዛሬዎች ደሞ የእፉኝት ልጆች ከዕውቀት ነፃ ብኩኖች ሆነን የጦለገ ሀሳብ እቅድ እንቃዣለን...እናምጣለን...የማይወለድ ከንቱ ኪሳራ ምጥ....
አሁን ላይ ይወለዳል ጀግና ... ዛሬ አንድ ሌሎች ሰወች ይወለዳሉ...ሰው የነበሩት በነበር እንዳሁኖቹ እንደ እኛ
ኢትዮጵያውያን ፤ እኛ ጀግኖቹ ባለታሪኮቹ
ስንፈልግ አሮጊት ወግረን እንገድላለን ፤ ሲያምረን ክቡር የሰው ልጅን ከነህይወቱ እናቃጥላለን ፤ ስንሻ የጎጥና የጎሳ በረት ሰርተን እርስ በእርስ እንጋደላለን ፤ ሆዳችንን በቅጡ ሳንሞላ በጦር መሳሪያ እንጨፋጨፋለን ፤ በኑሮ ተወደደ ሰበብ መብታችንን መጠየቅ ሲገባን ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሚም እየሰራን እንለፋደዳለን ፤ መንግስት የዳቦና እንጀራ ጥያቄ እንዳነጠይቀው መነጋገሪያ ርእስ ሲፈጥርልን እንደ ግሪሳ ተሰብስበን አጀንዳ እናራግባለን ፣ ይህን ሁሉ ውርደት እያየን "ታሪካችን የ3ሺህ ዓመት ነው" እያልን እንመፃደቃለን ፤ ይህ ሁሉ ሲሆን የሀይማኖት ተቋማት የሰውን ልጅ መንፈሳዊ ልዕልና ማበልፀግ ሲገባቸው ገንዘብ እየለቀሙ ፣ ህንፃ እየገነቡ ፣ ይዞታቸውን እያስፋፉ መንፈሳዊ ያልሆኑ ደሀ ሀይማኖተኛችን ይፈለፍላሉ ...
ወዲያ ማዶ ደግሞ ... ፖለቲከኛው ወራዳ ከፋፋይ ነው ፤ ምሁሩ አድርባይ ነው ፤ ባለስልጣኑ ሌባ ነው ፤ ነጋዴው ስግብግብ ነው ፤ ጋዜጠኛው በቀቀን ነው ፤ መምህሩ መሀይም ነው ፤ የሀይማኖት አባት ተብዬዎች ነገር ማብረድ ትተው የጦርነት አታሞ ይደልቃሉ። የጎበዝ አለቆች በየሰፈሩ ህዝብን እንደፈለጉ ያርዳሉ። ከልካይ የላቸውም። ሃይባይ የላቸውም። ይህ ሁሉ ሲደረግ ቆመን እናያለን። የዳር ተመልካች ነን። ምንም አንጠይቅም። ግድም አይሰጠንም ፤ ርህራሄ የሚባል እውስጣችን የለም ፤ ፤ ለሌላው አንቆምም ፤ ቆም ብለን ዙሪያችንን አናይም ፤ ለመብት ጥያቄአችን ስንዝር አንጓዝም። አንተሳሰብም።
ምድር ላይ እራሳችን ለፈጠርናቸው እነዚህ ሁሉ ሰውሰራሽ ችግሮች መፍትሄ ከምድር የሚበቅል ወይ ከሰማይ የሚዘንብ ይመስለናል።
ታዲያ ደንቆሮ ህዝብ ከዚህ ውጪ ምን ሊመስል ይችላል ?
ኤሎዬ ኤሎዬ...ቃየል ወንድሙ...ዮዳዊ መጥፎ ግብርና ምግባር ....ያደፈ ስብህና የከረፋ ብሔርተኝነት....
ይከስማል .....
ሰው አሁን ይወለዳል !!...
የዶሮ ሻኛ ከመርካቶ ዳኒ በሉ እንቀባበል
እ'ደ የገደል ማሚቱ ...
@fungafiker የሠማ ላልሠማ ሼር
1.0K views15:18