ስለምወድሽ ነው! (ፉአድ ሙና) . ረመዳን ሊደርስ ፣ የቀሩትን ቀናት ወደታች ‘ሚቆጥር፣ ከመስጂዱ ቅጥር ተለጥፎ ካለው ፣ ሆድ የሚያስብስ ቁጥር፣ ከፊት ተገትሬ ፣ በቦዘዘ አይኔ ከገፄ ‘ምስልሽ፣ ትካዜ ‘ሚገባኝ ፣ በጥልቀት ሳስበው የስርቆቴ እንደሆንሽ፣ ልቤ ፍርሀት ወርሶት ፣ ሀዘን ‘ሚተኩሰው፣ ስለምወድድድሽ ነው!! . ላንቺ ያለኝ ፍቅር ፣ በይሁንታሽ ብርታት በድፍረት አብቦ፣ የጌታዬን ትዕዛዝ ፣ የጣሰው ያስጣሰሽ ፣ በወንጀል ተከቦ፣ በትዳር ሊያነፃሽ ፣ አቅም ቢደቁሰው ፣ እድሜ ቢሸብበው፣ ስህተቱን እያየ ፣የገባው ከጥፋት ፣አንቺን ከብዶት መተው፣ ለሌላ እኮ አይደለም ስለሚወድድድሽ ነው። . ከመስጂዱ ቅጥር ፣ ቁጥሩ ላይ አፍጥጬ፣ ስለ‘ኔ እና አንቺ ፣ ወሰንኩኝ ቆርጬ። ረመዳን ደርሶ ፣ መስፈሪያ ሲቀየር ፣ ስትታይ ጨረቃ፣ ኢድ እስከሚበሰር ፣ በተክቢር ተጠምቀን ፣ ፆሙ እስኪያበቃ፣ አይንሽን አላይም ፣ ድምፄን አትሰሚም ፣ መልዕክቴም አይደርስሽ፣ ወሩን ክበሪበት ፣ ከጌታሽ ታረቂ ፣ ይበተን ወንጀልሽ። . አዎን ታረቂበት! የሺ ወራት ምንዳ በሚታደልበት፣ የወንጀል ቅጣቱም ከፍፍፍ በሚልበት፣ ህዝቡ ተሰብስቦ በእጥፍ ሲከፈለው ፣ ለሞከራት ስራ፣ በባዶ እንዳትወጪ፣ ከሳሪ እንዳትሆኚ ፣ ቀርበሽ ለመከራ፣ ባዳ ወንድ በማየት ፣ ወንጀልሽ እንዳይገዝፍ ፣ በልጦ ከተራራ፣ በተራውሂ ሰበብ ፣ወጥተሽ አታግኚኝ፣ አትደውዪ አደራ! ልብሽ ክፉ አያስብ ፣ ሀሳቤን ተረጂ፣ ለነገ እጣፈንታሽ ፣ ብጠላ አይጨንቀኝም፣ ባፈቅር ነው እንጂ። አማኝ በአንድነት ከትቶ ከመስጂዱ ፣ ሲዘረገፍ እንባ፣ የአላህ ቃል ሲነበብ ፣ እዝነቱ ሲንቧቧ፣ ምንዳ እንካችሁ ሲባል ፣ ያለ አንዳች ገደብ ፣ያለ ምንም ኮታ፣ አምልኮሽ ላይ በርቺ ፣ ስርዓቱን ጥሰሽ አታግኚኝ ማታ። ከባሪያው መጠማት ፣ መራብ ግድ ከሌለው ፣ ከአንድዬ ተጋፍተን፣ በባዶ ሆዳችን ፣ ከአምልኮ ተናጥበን ፣ አንገናኝም ቀን፣ አደራ እንዳትረሺ! አፈቀርኩኝ ያለ ፍቅሩን አይበድልም ፣ በልጦበት ጥማቱ፣ የእርሷ መደሰት ነው ፣ የሷ ደህንነት ነው ፣ የዘወትር ጭንቀቱ። አፈቀርኩ ብያለሁ ፣ አንቺው ነሽ ስስቴ፣ ከአንቺ የነገ አለም ፣ አይበልጥም ስሜቴ። መቼም አልረሳሽም ፣ ነገም ሌላ ቀን ነው፣ ይህን የምለው ግን፣ አደራ እንዳትረሺ ስለምወድድድሽ ነው። . ታዲያ ግን የኔ አለም ፣ በፆም ዝለሽ ውለሽ ፣ ማታ ስታፈጥሪ፣ እጅሽን ከፍፍፍ አ‘ርገሽ ፣በእንባሽ እየታጠብሽ ፣ ስማችንን ጥሪ። እባክህን በይው በእዝነትህ በይው የከበደን ትዳር ደርሶ እንዲገራ ፣ እንድትሆኝ ሀላሌ፣ ያ ረብ ፣ ያ ረብ በይ ፣ እንዳትረሺው ሁሌ። ይህን ግን የምለው አደራ አስታውሺ ፣ ስለምወድድድሽ ነው። . @fuadmu @fuadmu ለአስተያየትዎ @fuadmubot 2.3K views16:41