በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ማለፊያ ነጥብ ማምጣት ላልቻሉ ተማሪዎች የማካካሻ ትምህርት (Remedial) ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ወስኗል። በሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ታህሳስ 24/2016 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የማካካሻ ትምህርት ለሚሰጡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከው ደብዳቤ ፤ የማካካሻ ትምህርቱ ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲሰጥ ያዛል። በዚህም ተቋማቱ ከጥር 1 ጀምሮ በቀሩት ወራት ትምህርቱን ውጤታማ በሆነ መንገድ መስጠት እንዳለባቸው ተገልጿል። Via Tikvah @Free_Education_Ethiopia Stay Safe! 12.8K viewsπ, 17:26