የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲሱን የጂንካ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃ ህንጻ እና ድጋፍ ሰጪ መሰረተ ልማቶች በዛሬው ዕለት በደማቅ ስነ-ስረዓት አስመረቀ። በ3500 ካሬ ስፋት ላይ ያረፈው ይህ ዘመናዊ መሰረተ ልማት ወደ ከተማዋ የሚጓዙ መንገደኞችን ምቾት ከፍ የሚያደርግና የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት በከፍተኛ መልኩ የሚያግዝ ነው። ውድ ክቡራን መንገደኞቻችን ወደየትኛውም የዓለም ጫፍ ጉዞዎን ማድረግ ሲያሻዎ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ ትኬት ቢሮ በአካል በመሄድ አልያም የሞባይል መተግበሪያችንን ወይም ድረገጻችንን በመጠቀም ትኬትዎን ገዝተው የማይረሳ ጉዞ ያድርጉ። #የኢትዮጵያአየርመንገድ 14.4K views08:55