የአንጋፋው የኢትዮጵያ አቪዬሽን ታሪክ አብነት የሆነችው እና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ ተገጣጥማ በሀገሪቱ ሰማይ ላይ ናኝታ የነበረችው “ፀሐይ” አውሮፕላን ከበርካታ ዓመታት በኋላ ለሀገሯ እንደምትበቃ በመስማታችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶናል።
ይህች አውሮፕላን ሀገራችን ዛሬ ለደረሰችበት የአቪዬሽን ዕድገት ፈር ቀዳጅ ከመሆኗም በላይ ለአቪዬሽኑ መስክ ዕደገት በየዘመናቱ ያለንን ቀናኢነት ማሳያ ምልክትም ናት። ይህች ብርቅዬ ታሪካዊ አውሮፕላን ለሀገሯ እንድትበቃ መንግስትን ጨምሮ ማንኛውንም ዓይነት አበርክቶ ለነበራቸው አካላት ሁሉ ከፍተኛ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ