የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዓመቱ በሚከናወነው የብሪክስ አባል ሀገራት የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የ2024 ሽልማት ላይ “Corporate Sustainability Achievement Award” አሸናፊ ሆነ። ሽልማቱ በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ለሚኖረው የንግድ ትስስር፣ የአፈፃፀም ልህቀት እና ፈጠራ ዕውቅና የሚሰጥ ነው። የብሪክስ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት በአባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ የንግድና የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴዎችን ለማበረታታት እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም የተቋቋመ ምክር ቤት ነው። https://rb.gy/o2v7ym 15.4K views15:33