ነዳጅ መንግሥት የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክ ክፍያ እንዲሆን መወሰኑን የመንግሥት ትራንስፖርት ሚንስቴርና ንግድ ሚንስቴር ትናንት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ከሐምሌ 2014 ዓ፣ም ጀምሮ በ"ቴሌ ብር" ክፍያ የሚፈጽሙት የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ብቻ ናቸው። ሆኖም ሁሉም ተሽከርካሪዎች በቅርብ ቀናት ውስጥ የኤሌክትሮኒክ ክፍያ እንዲጀምሩ እንደተወሰነ ሚንስቴሮቹ መናገራቸውን ዘገባዎች ጠቅሰዋል። መንግሥት ሌሎች የኤሌክትሪክ ክፍያ አማራጮችን ለመተግበር እንዳሰበም በመግለጫው ላይ ተገልጧል ሲል ዋዜማ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል። @EthioipaNews 4.0K views06:35