Get Mystery Box with random crypto!

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ለአብራሪነት እና ለቴክኒሽያን | ኢትዮ Students News

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ለአብራሪነት እና ለቴክኒሽያንነት ሙያ የወጣ የቅጠር ማስተዋቂያ

. አጠቃላይ መመዘኛ
- ዜግነት ኢትዮጵያ የሆነ/ነች፣
- ለህገ-መንግስቱ ተገዢ የሆነ/ነች፣
- መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ላት፣
- ዕድሜ ከ18-24 የሆነ/ነች፣
- ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያወጣውን የጤንነት መመዘኛ መስፈርት የሚያሟላ/የምታሟላ፣
- የወንጀል ጥፋት ሪከርድ የሌለበት/ባት ስለመሆኑ ከአካባቢው ቀበሌ ወይም ፖሊስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
- ከአሁን በፊት የመከላከያ ወይም የፖሊስ ሰራዊት አባል ያልነበረ/ች፣

የትምህርትና ሌሎች መመዘኛዎች

2.1. ለአብራሪዎች መመልመያ መስፈርቶች
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ/ሆና በ2012 እና በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ወስዶ/ወስዳ አጠቃላይ ውጤት 350 እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዘኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ የትምህርት አይነት አማካኝ ውጤት 70% እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት፣
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰደበትን/የወሰደችበትን የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናል እና ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
- ቁመት 1.65ሜ እና ከዛ በላይ የሆነ/የሆነች፣
- ክብደት ከ50-60 ኪ.ግ የሆነ/የሆነች፣
- የአየር ኃይል አካዳሚን የመግቢያ ፈተና ወስዶ/ዳ ማለፍ የሚችል/የምትችል፣

2.2. የቴክኒሽያኖች መመልመያ መስፈርቶች
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ/ና በ2012 እና በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዶ/ዳ አማካይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዘኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ ትምህርት አማካኝ ውጤት 60% እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት፣
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰደበትን/የወሰደችበትን የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናል እና ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
- ቁመት 1.65ሜ እና ከዛ በላይ የሆነ/የሆነች፣
- ክብደት ከ50-60 ኪ.ግ የሆነ/የሆነች፣
- የአየር ኃይል አካዳሚን የመግቢያ ፈተና ወስዶ/ዳ ማለፍ የሚችል/፣የምትችል

የምዝገባ ቦታ
- ለአዲስ አበባ ተመዝጋቢዎች፡- አምባሳደር አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ መከላከያ ሚኒስቴር ዋና መ/ቤት ብሄራዊ ተጠባባቂ ኃይል ማደራጃ እና ማስተባበሪያ ቢሮ፣
- ለድሬደዋ መስተዳድር ተመዝጋቢዎች፡- ድሬደዋ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለአማራ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃን፣ እና ደሴ ከተሞች በሚገኙ የፀጥታ ዘርፍ ቢሮዎች፣
- ለኦሮሚያ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ባሌ-ሮቤ፣ ጅማ፣ ነቀምት፣ ደምቢ ዶሎ፣ አምቦ፣ ቢሾፍቱ፣ አዳማ፣ ወሊሶ ከተሞች በሚገኙ የፀጥታ ዘርፍ ቢሮዎች፣
- ለደቡብ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና(ዋቻሞ) በሚገኙ የፀጥታ ዘርፍ ቢሮዎች፣
- ለአፋር ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ሰመራ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለሱማሌ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ጅግጅጋ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለሐረሪ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ሐረሪ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- አሶሳ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለጋምቤላ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ጋምቤላ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለሲዳማ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ሐዋሳ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለደቡብ ምዕራብ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ቦንጋ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ ይሆናል፡፡

የምዝገባ ጊዜ
ከግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 20 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ባሉ ተከታታይ የስራ ቀናት መሆኑን እንገልፃለን፡፡

• ይቀላቀሉን •
https://t.me/+2g72gKcjS_E4Mjdk
https://t.me/+2g72gKcjS_E4Mjdk