#AddisAbaba
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የማውጣት ስነስርዓት ወደ ዓርብ ተሻገረ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ14ኛ ዙር የጋራ መኖርያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ስነስርዓት ነገ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ/ም እንደሚካሄድ ገልጾ ነበር።
ነገር ግን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠራው ስብሰባ ምክንያት የእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱ ወደ ዓርብ ሃምሌ 1 ቀን 2014 የተዛወረ መሆኑን አስተዳደሩ አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፥ ለተፈጠረው የፕሮግራም ለውጥ ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን ታዛቢዎች፣ ባለዕድለኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የሚዲያ አካላት በተለዋጩ ፕሮግራም እንዲገኙ (ማለትም ዓርብ) መልዕክት አስተላልፏል።
@Esatethiopiantv
@Esatethiopiantv