Get Mystery Box with random crypto!

ለእርሻ፣ ለኮንስትራክሽን እና ተያያዥ አገልግሎቶች የሚውሉ ትራክተሮች እና ከባድ ተሽከርካሪዎችን ወ | ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

ለእርሻ፣ ለኮንስትራክሽን እና ተያያዥ አገልግሎቶች የሚውሉ ትራክተሮች እና ከባድ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ እንደተከለከሉ አስመጪዎች መናገራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነበበን

ይህም የሆነው ካለምንም መመርያ ሲሆን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት "የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም" እንዳላቸው ገልጸዋል። ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል።

ከሁሉም ግር የሚለው ደግሞ በቅርቡ በከተሞች በእንስሳት የታገዘ ትራንስፖርት እንዲኖር ስራ እየሰራ እንደሆነ የጠቆመው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከባድ ተሽከርካሪዎች በኤሌክትሪክ እንዲሰሩ መጠበቁ ነው።

በኤሌክትሪክ የሚሰራ ትራክተር? ገልባጭ መኪና? ግሬደር? ቡልዶዘር?

ታድያ ይህ እየሆነ ያለው በቢልዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ ለጫካ ፕሮጀክት እየፈሰሰ፣ ተጨማሪ በመቶ ሚልዮን ዶላሮች የሚቆጠር ደግሞ ለከተማ ማስዋብ እና ለቱሪዝም ስፍራዎች ግንባታ እየዋለ ባለበት ወቅት ነው።

ነዳጅ ለማስገባት የዶላር በእጅጉ መመናመን እንዳለ እንረዳለን፣ ግን በአንድ በኩል ለወደፊት ሊቆዩ የሚችሉ የከተማ ማስዋብ ፕሮጀክቶች ላይ ገንዘብ እየፈሰሰ፣ በዚህ በኩል ደግሞ ያውም ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ የሆኑትን ግብርናን እና ግንባታን የሚያከናውኑ ቅንጡ ያልሆኑ ተሽከርካሪዎችን መከልከል ምን ያህል misplaced priorities እንዳሉብን ማሳያ ነው።

@EliasMeseret