Get Mystery Box with random crypto!

13ኛ ዙር 20/80 ኮንዶሚኒየም ባለቤቶች መብት ሞጋች ህብረት

የቴሌግራም ቻናል አርማ dfdfhf — 13ኛ ዙር 20/80 ኮንዶሚኒየም ባለቤቶች መብት ሞጋች ህብረት 1
የቴሌግራም ቻናል አርማ dfdfhf — 13ኛ ዙር 20/80 ኮንዶሚኒየም ባለቤቶች መብት ሞጋች ህብረት
የሰርጥ አድራሻ: @dfdfhf
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.81K
የሰርጥ መግለጫ

በአብሮነት በጋራ በሰላም በመተሳሰብ በመደጋገፍ የተሻለ መኖሪያ እንፍጠር

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-26 17:43:00
3.0K viewsTewodros Eshetu, 14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-15 22:33:11 ነዋሪዎችን ያማረሩት ጫኝ እና አውራጆች ፦

ከቲክቫህ ቤተሰብ አባል ፦

" በአዲስ አበባ ከተማ ላይ በሁሉም ሰፈር ማለት ይቻላል በህገወጥ ጫኝና አውራጆች በሚጠየቅ የተጋነነ ክፍያ ምክንያት ዕቃ መኪና ላይ መጫንም ሆነ ማውረድ አዳጋች ሆኗል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ እነዚህ ህገ ወጦች ላይ እርምጃ በመውሰድ ህብረተሰቡን ሊታደግ ይገባል።

ሰው ተሰቃይቷል ፤ ህዝቡ ተበሳጭቷል ፤ ጉረቤትህ እና ልጆችህ እንኳ ተባብረው ሊያራግፉልህ እድል አይሰጡም።

እነዚህ ወጣቶች ሌላው በመቶ ብር ሚያራግፈውን እነሱ ቢያንስ እስከ 3 ሺ ብር ይጠይቃሉ። "

ከሰሞኑን ከዚህ ነዋሪዎችን እያማረረ ካለው ህገወጥ ድርጊት ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ለሸገር FM 102.1 ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል አሳውቋል።

በአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ፥

" ብዙ ችግር ነው ያለው። ለምሳሌ ፦

ቁሳቁሱን እኛ ብቻ ነን የምናወርደው ፤ የምንጭነው ብለው እራሳቸው ይወስናሉ በሰው ንብረት።

ተመጣጣኝ ክፍያ አይጠይቁም።

እርስ በእርስም የሚጣሉበት ሁኔታ አለ፤ በዚህም ንብረት ይወድማል አካል ጉዳት ይደርሳል። ምንም በማያገባው እዛ ባለው ግለሰብ ንብረት ላይ ጭምር ጉዳት ይደርሳል።

ግለሰቦችን ማጨነቅ አለ እኛ ካላወረድነው እናወድመዋልን የሚሉም አሉ።

ይሄ እጅግ በጣም ከባድ ነገር ነው። ስለዚህ ይሄን ስራ የሚሰሩ ሰዎች ተለይተው ህብረተሰቡ ለፖሊስ መረጃ በመስጠት አደብ እንዲገዙ መደረግ መቻል አለበት ካለበለዚያ ከባድ ስጋት ነው የሚሆኑት። " ብለዋል።

ፖሊስም የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በህገወጥ ጫኝ እና አውራጆች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ምክትል ኮማንደር ማርቆስ አሳውቀዋል።

ም/ኮማንደር ማርቆስ ፦

" በለሚኩራ ክ/ከተማ በ6 ወር በ21 መዝገቦች 80 ተከሳሾች ይዘን ምርመራ እያጣራን ነው። በተመሳሳይ በ12 መዝገቦች 45 ተጠርጣሪዎች ማረሚያ ቤት ወርደው ጉዳያቸውን በህግ እንዲከታተሉ እየተደረገ ነው።

በቦሌ ክ/ከተማ በ10 መዝገቦች 63 ተከሳሾች ላይ ክስ ተመስርቷል። 62ቱ ተይዘዋል። እነዚህም ምርመራ እየተጣራባቸው ነው።

ንፋስስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ሰፈራ የሚባል አካባቢ ባለፈው ወር የተሰራ ስራ በቀን 21/7/2014 ዓ/ም በአንድ መዝገብ 10 ተከሳሾች ይዘን ምርመራ እያጣራን ነው።

በለቡ ፖሊስ ጣቢያ ፤ ሆፕ ዩኒቨርሲቲ የሚባል አለ እዛ አፓርታማ ቤቶች አሉ እዛ የሚገቡ ሰዎች ላይ ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ በአንድ መዝገብ 13 ተጠርጣሪዎች ተይዘው በ4ቱ ላክ ሁለት ሁለት ወር እንዲወሰንባቸው ተደርጓል " ሲሉ አስረድተዋል።

" አንዳንድ ስራቸውን በአግባቡ የሚሰሩ ጫኝና አራጆች አሉ ፤ በቅርቡም ጥይቶች ተጭነው እስከማጋለጥ የደረሱ መኖራቸውን ተመልክተናል " ያሉት ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ያልተገባ ስራ የሚሰሩትን ፤ ወደ ህግ ከማቅረብ ይልቅ #ተስማሙ የሚሉ የፖሊስ አባላትን ህብረተሰቡ ሲመለከት በ991 ነፃ የስልክ መስመር እና በ 0111110111 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ከሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ጥሪ አቅርበዋል።
3.9K viewsTewodros Eshetu, 19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-14 19:59:49
3.4K viewsTewodros Eshetu, 16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-31 11:00:51 ቁልፍ ያልወሰዱ የ20/80 እና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ዕድለኞች በቀናት ውስጥ እንዲረከቡ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ
.
በተለያዩ የግንባታ ሳይቶች ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ግንባታቸው ተጠናቆ ቁልፍ እንዲወሰዱ የተነገራቸው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድለኞች ባለመምጣታቸው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በቀናት ውስጥ ቁልፍ እንዲወስዱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡ ኮርፖሬሽኑ ቁልፍ ላልተወሰደባቸው ቤቶች የሚያደርገውን ጥበቃ እንደሚያነሳ አስታውቋል፡፡

የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚገኙባቸው ፕሮጀክት ሳይቶች በሙሉ የተለጠፈው የኮርፖሬሽኑ ማስጠንቀቂያ፣ የሕንፃና የቤት ቁልፍ ርክክብ ከተጀመረ ብዙ ወራት ቢቆጠሩም ነዋሪው ቤቱን ተረክቦ እያደሰና እየገባ አለመሆኑን ይገልጻል፡፡ በዚህም ምክንያት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቶች ለተለያዩ ችግሮች እየተዳረጉ በመሆናቸው፣ ነዋሪዎች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስከ የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ መጥተው ቁልፍ እንዲረከቡ ያሳስባል፡፡ በተቀመጠው ቀነ ገደብ ውስጥ ቁልፍ የማይረከቡ ዕድለኞች ቤቶችን በተመለከተም፣ የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቶች ኃላፊነት እንደማይወስዱ ተገልጿል፡፡

ይህ ዓይነቱ ማስጠንቀቂያ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ባለባቸው እንደ ኮዬ ፈጬ፣ መሪ ሎቄና አያት ለመሳሰሉ 15 ሳይቶች እንደተሰጠ ለሪፖርተር የተናገሩት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አውራሪስ ከበደ፣ በእነዚህ ሳይቶች ውስጥ ለነዋሪዎች ርክክብ ደረጃ የደረሱ ከ55 ሺሕ የማያንሱ ቤቶች እንዳሉ አስረድተዋል፡፡

ይሁንና አብዛኛዎቹ ዕድለኞች ቁልፍ እንዲረከቡ በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ሊረከቡ አልቻሉም፡፡ ዳይሬክተሩ ኮዬ ፈጬ ፕሮጀክት አሥርን በምሳሌነት አንስተው፣ በፕሮጀክቱ ለርክክብ የተጠናቀቁ 9,000 ያህል ቤቶች ቢኖሩም መጥተው ማፅዳት እንዲጀመርና ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሻገሩ ጥሪ ከቀረበላቸው ነዋሪዎች ውስጥ የመጡት 4,000 አይሞሉም ብለዋል፡፡

ዕድለኞች የእነዚህን ቤቶች ቁልፍ እንዲረከቡ ጥሪ ከተደረገላቸው በኋላ እንደ ቀለም መቀባት ያሉ ቀሪ ሥራዎችን በራሳቸው ማጠናቀቅ እንዳለባቸው ያስረዱት አቶ አውራሪስ፣ ‹‹ያላለቁትንም ቢሆን ተረክበው ማሟላት ያለብንን እያሟላን እንሰጣቸዋለን፤›› ብለዋል፡፡

ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ቤቶቹ ከተጠናቀቁ በኋላ ያለ ባለቤት ሲቀመጡ ዕቃዎች የሚሰረቁበት አጋጣሚ እንዳለ ገልጸው፣ አሁን ኮርፖሬሽኑ የቀጠራቸው ጥበቃዎች ይኼንን እየጠበቁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ዕድለኞች ቁልፍ እንዲረከቡ በተቀመጠው ቀነ ገደብ ውስጥ ካልመጡ ኮርፖሬሽኑ ጥበቃዎቹን እንደሚያነሳ አስታውቀዋል፡፡

ቁልፍ አልተወሰደባቸውም ተብለው ቅሬታ የቀረበባቸው እነዚህ ቤቶች በ2011 ዓ.ም. በወጣው በ13ኛው ዙር የ20/80 ዕጣ፣ በሁለተኛው ዙር የ40/80 ዕጣ፣ እንዲሁም እንደ የልማት ተነሺነት ባሉ ልዩ ልዩ ምክንያቶች ለነዋሪዎች የተሰጡ ናቸው፡፡ በተለመደው አሠራር መሠረት ነዋሪዎቹ ቁልፍ በመረከብ በየብሎኩ በኮሚቴ በመደራጀት ጥበቃ ማቆምን ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎችን ይሠራሉ፡፡ በቤቶቻቸው ግንባታ ላይ ጉድለት ተፈጥሮም ከሆነ ቅሬታ እንዲያቀርቡ ይደረጋል፡፡

ይሁንና እነዚህን ቤቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ዕድለኞች ቁልፍ እንዲረከቡ ቢጠየቅም ብዙዎቹ እንደ ውኃ፣ መብራትና መንገድ ያሉ የመሠረተ ልማት አቅርቦቶች አልተሟሉላቸውም፡፡

በኮዬ ፈጬ ፕሮጀክት አሥር የቁልፍ ርክክብ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አይጠገብ ውዴ እንደሚያስረዱት፣ በዚህ ፕሮጀክት ሥር ያሉ ቤቶች የመፀዳጃ ቤት መፋሰሻ ስላልተሠራ ነዋሪዎች ቁልፉን ቢረከቡም ገብተው መኖር አይችሉም፡፡ ይሁንና እንዲህ ዓይነት የመሠረተ ልማት ጉዳዮችን የሚመለከተው እንደ ውኃና ፍሳሽ ያሉ ተቋማትን እንጂ፣ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱን አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡

አንዳንድ ነዋሪዎች ቁልፍ ላለመረከባቸው ይኼ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል የጠቆሙት አቶ አይጠገብ፣ ከባንክ ጋር የክፍያ ፕሮሰስ ያልጨረሱ እንዳሉም ተናግረዋል፡፡ ሰብሳቢው፣ ‹‹ይሁንና በተለይ አርሶ አደር ነዋሪዎች ቁልፍ እንዲረከቡ ቢጠየቁም፣ ከተረከብን እንሰረቃለን በማለት ኃላፊነት ላለመውሰድ መንግሥት መብራትና ውኃን አጠናቆ ያስረክበን ይላሉ፤›› ብለዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አውራሪስ በበኩላቸው የመሠረተ ልማት ሥራዎች ከተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን አስታውቀው፣ ‹‹ኃላፊነቱ የጋራ ነው መሆን ያለበት፣ እኛ ብቻ ቤቶቹን እየጠበቅን መቆየት የለብንም፤›› ብለዋል፡፡ (ሪፖርተር)
4.5K viewsTewodros Eshetu, 08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-22 13:34:48
5.9K viewsTewodros Eshetu, 10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-15 23:40:52
#የ20_80_ቤቶች
እጣ ያልወጣባቸው ከ30ሺህ በላይ የሚሆኑ ቤቶች ለ1997 ተመዝጋቢዎች በቅርቡ ይተላለፋሉ።

https://t.me/ethiohomesolutions
6.6K viewsTewodros Eshetu, 20:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ