Get Mystery Box with random crypto!

የወጋገን ባንክ የቀድሞፕሬዘዳንት አቶ አባይ መሀሪ መታሰራቸው ተሰማ። የወጋገን ባንክ የቀድሞ ፕ | Addis Merkato

የወጋገን ባንክ የቀድሞፕሬዘዳንት አቶ አባይ መሀሪ መታሰራቸው ተሰማ።

የወጋገን ባንክ የቀድሞ ፕሬዘዳንት እና ምክትል ፕሬዘዳንት ጨምሮ 8 የባንኩ የስራ ሃላፊዎች የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው ነበር፡፡

የቀድሞ ወጋገን ባንክ ፕሬዘዳንት ግንባታ ባልተካሄደበት ይዞታ ከ 88 ሚሊየን ብር በላይ በማበደር ተጠርጥረው ነበር።

እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች የባንኩ የስራ ሃላፊዎች ላይ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ክስ መስርቷል።

ዛሬ ጥር 19፣2013 ዓ/ም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ፀረ ሙስና ችሎት የተከሳሾችን ጉዳይ ለማየት የተሰየመ ሲሆን የወጋገን ባንክ ፕሬዘዳንት አቶ አባይ መሃሪም በችሎቱን ተገኝተዋል።

1ኛ ተከሳሽ አቶ አባይ መሃሪ ቋሚ አደራሻ እያለን ፌደራል ፖሊስ ሳንጠራ እንደ ማንኛውም ሰው በመገናኛ ብዙሃን ሰምተን በፍቃደኝነት መጥተናል ሲሉ በጠበቃቸው በኩል ለችሎቱ ተናግረዋል፡፡

በጡረታ ነው የምተዳደረው ያሉት አቶ አባይ መሀሪ ጡረታዬም ታግዶብኛ ሲሉ ለችሎቱ ተናግረዋል። ዋስትናም ሊጠበቅልኝ ይገባል ሲሉ ተከርክረዋል።

ፍርድ ቤቱ በዚህ ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለጥር 25፣2013 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።

የቀድሞ የወጋገን ባንክ ፕሬዘዳንት አቶ አባይ መሃሪ ግን እስከዛው ባሉበት እንዲቆዩ ሲል አዟል፡፡

via Sheger

#የዛሬ_መረጃ #አዲስመረጃ #ትኩስ_መረጃ