የካርል አደባባይ በትራፊክ መብራት ሊቀየር ነው በአዲስ አበባ ከተማ ከብስራተ ገብርኤል ወደ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው የካርል አደባባይ የትራፊክ ፍሰቱን የበለጠ ለማሳለጥ ወደ ትራፊክ ሲግናል መብራት ሊቀየር ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን አሁን ላይ በአካባቢው ያለውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨነናቅ ችግር ለመፍታት የካርል አደባባይን ወደ ትራፊክ መብራት ለመቀየር ዛሬ ምሽት የግንባታ ስራ ጀምሯል፡፡ 8.5K viewsedited 16:56