Get Mystery Box with random crypto!

የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ

የቴሌግራም ቻናል አርማ commercegebi — የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ
የቴሌግራም ቻናል አርማ commercegebi — የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ
የሰርጥ አድራሻ: @commercegebi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 377
የሰርጥ መግለጫ

ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው ። በዚህ ቻናል ላይ ግቢ ጉባኤውን በተመለከተ መልእክቶች፣መንፈሳዊ ጽሑፎች ፣ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎች መሰል መልእክቶች ይተላለፉበታል ፡፡
ያሏችሁን ጥያቄዎችና አስተያየት በዚህ bot ይላኩልን👉 @CommGibiGubae_bot

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

3

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-26 08:56:26
@commercegebi
19 views05:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 08:55:59 ​​ ቅዱስ ገብርኤል
ሐምሌ "19"

እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!

በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡

በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡

ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡

መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡

መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃኑ ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡

በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡

እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡

ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡

አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡

ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።

ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን
የቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት አይለየን፤ በቅዱስ ቂርቆስና በቅድስት ኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ: አ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ


@commercegebi
19 views05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 10:44:04
.
የኮርስ ትምህርት ለአዲስ ገቢ
1ኛ ዓመት ተማሪዎች


የትምህርተ ክርስትና መግቢያ

በሰዓቱ ተገኝተን የእግዚአብሔርን ቃል እንማር፣ ላልሰሙ ጓደኞቻችሁም እንድታሳውቁ በእመቤታችን ስም እናሳስባለን።

ዐርብ (ነገ) ሐምሌ 8፣
2014 ዓ.ም

ከ7:30 - 9:00


በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ

የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ
@commercegebi
167 views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 10:41:44
.
የኮርስ ትምህርት ለ2ኛ ዓመት
ተማሪዎች
(ማጠቃለያ)

ለ2ኛ ዓመት ተማሪዎች እስካሁን ሲሰጥ የነበረው የ "ነገረ ሃይማኖት" የኮርስ ትምህርት ማጠቃለያ (የመጨረሻው ክፍል) በነገው ዕለት ይኖረናል።

ዓርብ
ሐምሌ 8፣ 2014 ዓ.ም
ነገ
ከ7:30 - 9:00

ኮርሱን የምናጠናቅቅበት ዕለት ስለሆነ፣ ላልሰሙ ጓደኞቻችሁም እንድታሳውቁ በእመቤታችን ስም እናሳስባለን።

በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ

የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ
@commercegebi
138 views07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 11:14:33 የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ pinned « የዛሬው የአንደኛ እና የሁለተኛ አመት ተማሪዎች የኮርስ ትምህርት በፈተና ምክንያት አይኖርም፡፡ መልካም ፈተና ! @commercegebi»
08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 11:13:59 የዛሬው የአንደኛ እና የሁለተኛ አመት ተማሪዎች የኮርስ ትምህርት በፈተና ምክንያት አይኖርም፡፡

መልካም ፈተና !

@commercegebi
220 views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:12:45 የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ pinned a photo
08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:12:35 የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ pinned a photo
08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:11:56
.
የኮርስ ትምህርት ለአዲስ ገቢ
1ኛ ዓመት ተማሪዎች


የትምህርተ ክርስትና መግቢያ

የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት የጀመራችሁት ተከታታይ የኮርስ ትምህርት በነገው ዕለት ይቀጥላል።

ስለሆነም ሁላችንም በሰዓቱ ተገኝተን የእግዚአብሔርን ቃል እንማር፣ ላልሰሙ ጓደኞቻችሁም እንድታሳውቁ በእመቤታችን ስም እናሳስባለን።

ዐርብ (ነገ) ሐምሌ 1፣
2014 ዓ.ም

ከ7:30 - 9:00


በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ

የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ
@commercegebi
221 views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:10:27
.
የኮርስ ትምህርት ለ2ኛ ዓመት
ተማሪዎች


ነገረ ሃይማኖት

ሁላችንም ተጠራርተን በሰዓቱ እንገኝ። ላልሰሙ ጓደኞቻችን እናሰማ።

(ነገ)ዐርብ ሐምሌ 1፣ 2014 ዓ.ም

ከ7:30 - 9:00


በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ

የኮሜርስ ግቢ ጉባኤ
@commercegebi
154 views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ