ጣፋጭ ድል ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ========================== በ22ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ከሲዳማ ቡና ጋር ያገናኘው ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ85ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረው እጅግ ጣፋጭ ጎል መሪነቱን አጠናክሯል። በዚህም መሰረት ከተከታዮ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 5 ከፍ በማድረግ ለዋንጫ የሚያደርገው ግስጋሴ አጓጊ አርጎታል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን ባደረጋቸው 22 ጨዋታዎች 46 ነጠብ እና 19 ንፁህ ጎል በማስቆጠር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን እየመራ ይገኛል። 15.3K viewsBiniam zewdie, 18:50