2021-09-04 13:52:42
አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ ከአፍሪካ ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ ከአፍሪካ ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ።የአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና ዛሬ በሰጡት መግለጫ ዩኒቨርስቲው በርካታ ደረጃዎችን በማሻሻል ከአፍሪካ ምርጥ ዩኒቨርሲቲዎች ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል ብለዋል።ታይምስ ሃየር ኤጁኬሽን የተባለው ዓለም አቀፍ ዩኒቨርስቲዎች ደረጃ አውጪ ተቋም ትላንት ይፋ ባደረገው መሰረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደረጃው መገለጹንም ጠቅሰዋል።
በተቋሙ ደረጃ አሰጣጥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ 402ኛ ደረጃ ላይ ማስቀጠኑንም ፕሮፌሰር ጣሰው ገልጸዋል።
በመማር ማስተማር፣ ዩኒቨርስቲው የሚያስገባው ገቢና የጥናትና ምርምር ስራዎች ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለውድድሩ መስፈርት እንደነበሩ ተገልጿል። በዚህም ከ1 ሺ 600 በላይ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ተወዳድሮ በአፍሪካ 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል ብለዋል። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
"ዩኒቨርስቲው በዓለም አቀፍና በአህጉር ደረጃ ያሳየው መሻሻል በታሪኩ ትልቅ አፈጻጸም ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለውጤቱ መገኘት አስተማሪዎች፣ ተማሪዎችና የአስተዳደር ሰራተኞች ሚና ጉልህ እንደሆነ አስታውሰዋል። የደረጃው መሻሻል ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ያላትን ገጽታ ከማጉላት ባለፈ የበለጠ በመስራት ያነሳሳል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር እመቤት ሙሉጌታ በበኩላቸው ተቋሙ ደረጃውን የበለጠ ለማሻሻል በስትራቴጂ ተደግፎ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።በተለይም ጥናትና ምርምሮችን ማብዛት በስትራተጄው ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች መካከል ቀዳሚው መሆኑን መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የዩኒቨርስቲው አስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ማቲዎስ ኢንሰርሙ እንዳሉትም ዩኒቨርስቲው ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ በመሸጋገር ላይ መገኘቱ በዓለምና በአህጉር አቀፍ ደረጃ ራሱን ተወዳዳሪ ለማድረግ አወንታዊ አስተዋጽኦ አለው። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እኤአ 2020 በዩ ኤስ ኒውስ በተደረገ ዓለም አቀፍ ግምገማ በአፍሪካ 10ኛ ከዓለም ደግሞ 553ኛ ደረጃን ይዞ እንደነበር ይታወቃል።
@campus_life3
@campus_life3
3.7K views10:52