2022-05-27 08:03:55
የቀድሞ የቡታጅራ ድንቅ አጥቂ የነበረው ዳንኤል የይድረሱልኝ መልክት አስተላልፉዋል።
ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው ለኛ ኢትዮጲያውያን መረዳዳት ባህላችን/መገለጪያችን ነው።
▻ግድ ካልሆነ የሰው ፊት ይከብዳል የፈጣሪ እርዳታ ይበልጣል
ቀኑ ታህሳስ 28 2014 ነው ለገና በዓል ቤተሰብ ጥየቃ ከቃልቲ መነሐሪያ ዝዋይ ከዝዋይ ኢንሴኖ መዳረሻውን ከዛም አባቱን ለመጠየቅ ቡታጀራ ነበር ሰውኛ እቅዱ
እቅዱን እውን ለማድረግ ዶልፊን በሚባለው ተሽከርካሪ በክብር የጋቢና መሐል ቦታውን ይዞ ጉዞውን ጀመረ ለጉዞ የሚያካሄደውን መጽሐፍ እያነበበ ነበር ።
እንደ አርቲስት የአብስ ስራ ዳንኤል ገለጻ
በመጨረሻም ይላል አርቲስቱ በመጻፉ ተመስጬ ስለነበር ጉዞዬ መቂ ልንገባ መሆኑን ከረዳቱ የጀርባ ወሬ ሰምቼ ነው።
በትንሽ ቆይታ ቦኃላ በጉዞ ውስጥ ተጨማሪ ድምጽ የሰማው ወይኔ ወይኔ የሚል ለካስ የሹፌሩ ነው
ድንጋጤ በተሞላ ሰመመን ድፍን ጨለማ ታየኝ
ምን ያክል ሰዓት እንደሆነ ባላውቅም ስነቃ ራሴን ሆስፒታል ውስጥ አገኘሁት አንድ ወጣት ከፊቴ ቆሞ ተርፈሀል እያለ ስልክ ቁጥር ይጠቀኛል ህልም ቅዠት ህመም ጫጫታ ለቅሶ ይሰማኛል አዕምሮዬ ላይ የማይጠፋውን የናቴን ቁጥር ሰጥቼው ቤተሰብ ጋር ደውሎ ቤተሰብ መጣና ሪፈር ወደ ወራቤ ሆስፒታል ተጽፎን ነብሴን ለማትረፍ ወደ ወራቤ ሄድን በዛም ኤክስሬይ እና ሲቲ እስካን ምርመራ ተደርጎልኝ እዚህ ስለማንሰራው ወደ ሌላ ቦታ ሪፈር ይጻፍ አሉ ።
ጉዳቱ ምንድን ነው ሲባል እጁና አግሩ ነው ጭንቅላቱ ሆዱ ውስጥ ምንም ጉዳት የለበትም ሲባል ይሄማ ቀላል ነው ተብሎ ታዋቂ ውጌሻ ተጠርቶ በቤት ህክምናዬ መከታተል ጀመርኩኝ ግን አልሆነም
አንድ ነርስ ጓደኛም ነበረኝ አንቲፔንና ለኢንፌክሽን መድሐኒትና መርፌ እየሰጠኝ በወጌሻም እየታገዝኩኝ የተወሰኑ ቀኖች አለፉ የእጄ ጥሩ ለውጥ ሲያመጣ እግሬ ግን እንዳሰብኩት ጥንካሬውን ሳጣ ለዳግም ቼክ አፕ ምርመራ ወደ ቡታጅራ ሆስፒታል አመራው ምርመራ ተደርጎልኝ እግሬ የግድ ኦፕራሲዮን እንደሚያስፈልገው ዶክተሩ ነገሩኝ።
ጥቁር አንበሳ በሪፈር ላከኝና ወደ አዲስ አመራሁ ምርመራዎች እንደ አዲስ ተደርገውልኝ ኦፕራሲዮን እንዲሰራ ቀጠሮ ሰጡኝ ከሶስት እስከ አራት ዓመት እንዴ ዶክተር በህይወት ተርፌ ሶስት አራት ዓመት እንዴት ነው ያለ አንዳች ህክምና የሚቆየው ስለው የግል የሚሰሩ አራት አምስት መቶ ሺህ ይጨርሳል አለኝ
እሺ ብዬ ቀጠሮ አሲይዤ ወጣሁኝና ቀጥታ ወደ ወላይታ አመራው
በዛም እንደ አዲስ ተመርምሬ እንደውላለን ቀጠሮና ሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ ያስፈልጋል አሉኝ እሺ ስልካቹን ስጡኝ ስል እኛ ነን የምንደውለው ስራችን ነው አሉኝ
▻ ከወላይታ ከመጣው ሶስተኛው ወሬ ሲሆን ተመስገን ነው ከአልጋ ዊልቸር ከዊልቸር ክራንች ደረጃ ደርሻው ሞቼ ሞቼ ቢሆን ዛሬ ተረስቼ ነበር አምስት ወር አዲስ ህይወት ኖሬያለው ዳግም ዳንኤል ሆኛለሁ ተመስገን ፈጣሪዬ!!!
▻የተለያዩ ዶክተሮችን ሳማክር በግልም ቢሆን መሰራት አለብህ እየቆየ በሄደ ቁጥር ኢንፌክሽን ፈጥሮ ሌላ የካንስር ጣጣ እንዳያመጣ እያሉኝ ስለሆነ ግራ ተጋብቼ አለሁ ።
እኔ እና ቤተሰቦቼ ከአምላክ ጋር በመሆን የቻልነውን አደረግን አሁን ግን ደክሞን የእናተን እርዳታ አሸው
ለእህልሜ መሳካት እና ወደ የምወደው ሙያዬ ለመመለስ ቀዶ ጥገናውን ማድረግ ግዴታ ነው ያን ለማድረግ ግን ደከመኝ አቅም አነሰኝ
በምወደው የቲያትር ፊልም ሙያዬ የምሰራና የምማር ሲሆን በዘንድሮ መጨረሻ አልያም በቀጣዩ ዓመት የተፈሪ መኮንን የቲኤምኤስ ተመራቂም ነኝ ።
ፈጣሪ በተዓምር ሶስት ሰው ከሞተበት ለዛውም ጋቢና ላይ ካተረፈኝ ማያድነኝ ምንም ምክንያት የለም ከትላንት በተሻለ ዛሬ በፈጣሪዬ አምናለው ያድነኛልም ።
አሁን ላይ አራት ኪሎ በሚገኘው ዳኑ ሆስፒታል የይሰራልሀል ተስፋ ስላለኝ ራሴን በገንዘብ ለማዘጋጀት የግድ ሰው አስፈላጊ ነው ድኜ ወደ ምወደው ትልቅ ግብ ወዳለኝ ሁሉ ነገሬ ለመመለሰ ቆሜ መሔዴ የግድ ነው ና እንደ ቤተሰብ እንረዳዳ ብዬ ብቅ ብያለሁ።
▻በመጨረሻም የትውልድ ቀዬ ቡታጅራ ህዝብ ሆነ የኢትዮጲያ ህዝብ ከጎኔ እንደ ሚሆን ሙሉ ተስፋ አለኝ።
▻ቡታጅራዋች በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ የምትኖሩ ሁላችንም የተለመደው ሰው ተቸግሮ የመረዳዳት መገለጪያችን ለወንድማችን #ባምላክ_ዳንኤል ከፈጣሪ ጋር ወደ ቀድሞ ጤንነቱ የሚመለስበት ህክምና ያደርግ ዘንድ የአቅማችን በመደገፍ የተለመደው ትብብራችን አይለየው።
ለተጨማሪ
በአምላክ ዳንኤል የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁ.1000389222837
በአምላክ ዳንኤል የአቢሲኒያ ባንክ አካውንት ቀ. 96837078
በአምላክ ዳንኤል ስልክ ቁ.0911-54 73 35
1.2K viewsedited 05:03