Get Mystery Box with random crypto!

ባንካችን አቢሲንያ የአለም አቀፉን የሴቶች ቀን ማርች 8 በማስመልከት ለ 3ኛ ግዜ “ እችላለሁ “ | Bank of Abyssinia

ባንካችን አቢሲንያ የአለም አቀፉን የሴቶች ቀን ማርች 8 በማስመልከት ለ 3ኛ ግዜ “ እችላለሁ “ በሚል መሪ ቃል ልዩ ልዩ ዉድድሮችን ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 21 እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህ መርሀ ግብር ላይ በግጥም፣ በሙዚቃ፣ በቲክቶከሮች መካከል የሚደረግ ዉድድር የሚከናወን ይሆናል፡፡ ከዚህ በፊት ባንኩ በሁለት ዙር ባከናወናቸዉ የ “ እችላለሁ “ ዘመቻ በመጀመሪያዉ ዙር ለ 27 የስራ ፈጣሪ ሴቶች ለእያንዳንዳቸዉ 300,000 (ሶስት መቶ ሺ ብር ) በሁለተኛዉ ዙር ደግሞ ለ 50 የስራ ፈጣሪ ሴቶች ለእያንዳንዳቸዉ 500,000 (አምስት መቶ ሺ ብር ) በዝቅተኛ ወለድ ያለመያዣ ብድር አዘጋጅቶ ለባለእድለኞች መስጠቱ ይታወሳል፡፡
በዚህ ዙርም በተመሳሳይ ለ 50 የስራ ፈጣሪ ሴቶች ለእያንዳንዳቸዉ 500,000 (አምስት መቶ ሺ ብር ) ያዘጋጀን ሲሆን መስፈርቱን የምታሟሉ ሴቶች እንድትወዳደሩ እንጋብዛለን፡፡ ከባለፈው ዓመት የእድሉ ተጠቃሚዎች መካከልም ሁለቱ አሸናፊዎች ያሉትን ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
ዝርዝር የብድር እንዲሁም የመወዳደሪያ መስፈርቶችን ከዚህ በታች የሚገኘውን የቴልግራም ሊንክ ያግኙ፡፡
https://t.me/BoAEth/1146
#march8 #womansday #ican #Savings #enterpreneur
#BankofAbyssinia #Abyssinia #Banking #BankingService #Digital #DigitalEthiopia #DigitalPayment #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ