Get Mystery Box with random crypto!

Bahir Dar city communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ bahirdarcitycommunication — Bahir Dar city communication B
የቴሌግራም ቻናል አርማ bahirdarcitycommunication — Bahir Dar city communication
የሰርጥ አድራሻ: @bahirdarcitycommunication
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.57K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-15 19:59:57 ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የግንባታ ሒደትን ተመለከቱ! (ግንቦት 7/2015 ዓ.ም)
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በዛሬ ዕለት የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ቀሪ የግንባታ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ተመልክተዋል።

የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ዝቅተኛውን የፊፋ መስፈርት ማሟላት የሚያስችለውን የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃ ከፋለ የግንባታ ሒደቱ አበረታች ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው ቀሪ ስራዎችን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ የሰው ኃይልና አስፈላጊ ግብአት ማሟላት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

ርእሰ መስተዳድሩ አክለውም የስታዲየሙ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ተፈላጊውን አገልግሎት እንዲሰጥ የምናደርገውን ክትትል አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል ።
ምንጭ :- የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት
225 views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 19:59:56
222 views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 22:04:55 ቀን=06/09/2015ዓ፡ም
ባህርዳር ከተማ እግር ኳስ ክለብ ወሳኝ የሆነውን ሶስት ነጥብ አሳካ።
===
በዛሬው እለት በተካሄደው በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 24ተኛ ሳምንት መርሐግብር ባህርዳር ከተማ ከአዳማ ከተማን 1ለ0 በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የባህርዳር ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አደም አባስ ተቀይሮ በመግባት ከመረብ ማሳረፍ ሲችል ፤ ዉጤቱን ተከትሎም ባህርዳር ከተማ ነጥቡን ሀምሳ በማድረስ አንድ ጨዋታ ከሚቀረው የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አንድ ማጥበብ ችሏል።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://www.youtube.com/channel/UCNoAcvzPiExah4lyaAb6_BQ
https://t.me/Bahirdarcitycommunication
https://twitter.com/Bahirdarፐ
405 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 22:04:36
388 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 22:47:24
449 views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 22:47:14 ተማሪዎቻችን በቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት እየዳበሩ ነው።ዶ/ር ድረስ ሳህሉ የባህርዳር ከተማ ከንቲባ

በባህርዳር ከተማ የሚገኙ የግል እና የመንግስት ትምህርት ቤት የተማሪዎች ፈጠራ እግዚቪሽን በጣና ኃይቅ 2ኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤት እየተካሄደ ነው።

እየተካሄደ ያለውን የተማሪዎች የፈጠራ ስራ የተመለከቱት የባህርዳር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ድረስ ሳህሉ በልዩ ልዩ ፈጠራ ስራ የተሰሩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተማሪዎቻችን በቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት እየተጠናከሩ ስኬታማ ስራ እንደሚሰሩ አመላካች በመሆኑ ወደ ፊት ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

በከተማችን ባህርዳር ከሚገኙ 88 የ1ኛ ደረጃ ፣21 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የ83 1ኛ ደረጃ እና የ21 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የፈጠራ ስራቸውን በባዛር አውደ ርዕይ ለእይታ አቅርበው የፈጠራ ስራቸውን እንዲያሳድጉ በማሰብ ትምህርት መምሪያው ለትምህርት ጥራትና ለተማሪዎች ውጤታማነት አጋዥ የሆኑ ስራዎችን እየሰራ መሆኑንና በዚህም በርካታ ተማሪዎች ሁለንተናዊ የሆኑ ትልልቅ ፈጠራዎችን በመስራት ለነገ ሀገራዊ ግንባታ ተስፋ የሚሰጡ አመርቂ ስራዎችን እያሳዩ ይገኛሉ ሲሉ የትምህርት መምሪያው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ሰብለ ዘውዱ ገልፀዋል።

የባህርዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኃይለማርያም እሸቴ በበኩላቸው በተማሪዎቻችን እየተከናወነ ያለውን የቴክኖሎጅ ፈጠራ አሳድጎ ጥቅም ላይ እንዲውልና ዘላቂና ተደራሽ እንዲሆን አጠናክረን መስራት የወደፊት ተግባራችን ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://www.youtube.com/channel/UCNoAcvzPiExah4lyaAb6_BQ
https://t.me/Bahirdarcitycommunication
https://twitter.com/Bahirdarፐ
419 views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 21:59:38
355 views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 06:11:12
193 views03:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 06:11:00 ግንቦት 02/2015
የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት እና ሥራ ፕሮጀክት በባህርዳር ከተማ ለሚገኙ ሰሪ የዘርፉ ተጠቃሚዎች የንግድ ስራ ክህሎትና እቅድ ዝግጅት ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።

ስልጠናው የባህርዳር ከተማ ምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍቲኔት ጽ/ቤት ከሌሎች አጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በየክፍለ ከተማው ለተለዩና 1ሺ ለሚሆኑ ሰሪ ኃይሎች በንግድ ስራ ክህሎት እና በንግድ ስራ እቅድ አተገባበር ዙሪያ የተሰጠ ሲሆን በስልጠና ማጠቃለያ መድረኩ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸው ሰሪዎች የስኬት ጅማሮ ለተሳታፊዎቹ ቀርቧል።

ከዚህ ባለፈ የባህርዳር ከተማ ምግብ ዋስትና ሴፍቲኔት ጽ/ቤት በዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ዘርፍ የድጋፍ ማዕቀፍ ላይ ለመጀመሪያ ዙር ተጠቃሚዎች ውጤታማነት አመች የሆኑ ተግባራትን በማከናወን በኩል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ስለመሆኑና ስለፕሮጀክቱ አጠቃላይ አተገባበር ዙሪያ በጽ/ቤቱ የዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ምኒችል ጌቴ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ቀርቧል።

የንግድ ስራ ክህሎት እና የንግድ ስራ እቅድ አተገባበር ስልጠናው ተጠቃሚ የሆኑ ሰሪ ኃይሎች በበኩላቸው የምግብ ዋስትና ሴፍቲኔት ድጋፍ ከማግኘታቸው በፊት በከፋ የኑሮ ውጣ ውረድ ውስጥ የቆዩ መሆኑንና ሰርቶ የመለወጥ እድላቸው የተዘጋ እንደሆነ ተቀብለው በቀቢፀ ተስፋ የቆዩ መሆኑን ገልፀዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዚህ ፕሮጀክት ታቅፈው የቀጥታ ድጋፍና የልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚ ከሆኑ ጀምሮ ግን ራሳቸውን የመለወጥ ቤተሰባቸውን የመምራትና ከዚህ አልፎም ቁጠባ በመቆጠብም ሆነ በእድርና መሰል ማህበራዊ ተሳትፎዎች ጭምር በንቃት ተሳታፊ በመሆን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን በማሳደግ ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በዚህ ፕሮጀክት የትግበራ ስልጠና ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባህርዳር ከተማ ምግብ ዋስትና ሴፍቲኔት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እመቤት መንግስቱ እንደገለፁት የዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ተጠቃሚዎች በግል ወይም በቅጥር የስራ መስኮች ተሰማርተው ገቢያቸውን እንዲያሻሽሉ እና ሀብት ንብረት በማፍራት በኑሯቸው የሚገጥሟቸውን ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በራሳቸው ሃቅም መፍታት እንዲችሉ ከማድረግ ባለፈ ለከተማ ልማት መሻሻል ያለው ፋይዳ በቀላል የሚገመት አለመሆኑን እንስተዋል።

ስለሆነም ይህ ለበርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ህይወት መሻሻል ትልቅ ድርሻ ያለው ፕሮጀክት ለዘላቂ ልማት እንዲውል ከሰሪዎች ጀምሮ ሁሉም አጋርና ባለድርሻ አካል የጉዳዩን ሁለንተናዊ ጠቀሜታ በመረዳት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ቀጣይነት ያለው ስኬት ማስመዝገብ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://www.youtube.com/channel/UCNoAcvzPiExah4lyaAb6_BQ
https://t.me/Bahirdarcitycommunication
https://twitter.com/Bahirdarፐ
190 views03:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 23:28:51 ቀን=02/09/2015ዓ፡ም
የሴቶች፣ ህፃናትንና አረጋዉያንን ሁለንተናዊ ተሳትፎንና ተጠቃሚነት በተሻለ ደረጃ ለማረጋገጥ ሁሉም ተቋም በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለፀ።
===========
ግንቦት 2/2015ዓ፡ም የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የሴቶች ፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ2015 በጀት አመት የ3ኛ ሩብ አመት አቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ያካሄደ ሲሆን በግምገማዉ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የመምሪያዉ ሰራተኞች ፣የተለያዩ የሴት አደረጃጀቶች፣የአካል ጉዳተኞች ፌደሬሽ አመራሮች ፣የአረጋውያን ማህበር አደረጃጀቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አጋር አካላት ተገኝተዉበታል።

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://www.youtube.com/channel/UCNoAcvzPiExah4lyaAb6_BQ
https://t.me/Bahirdarcitycommunication
https://twitter.com/Bahirdarፐ
219 views20:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ