ገበሬው በጣም የሚወደው ፈረሱ ይታመምበትና ሀኪም ጠርቶ ያስመረምረዋል ። ሀኪሙም ፈረሱ አርጅቷል መድኃኒት እንስጠውና ከ3 ቀን በፊት ካልተሻለው ላንተም ሸክም ከሚሆን እንገለዋለን ብሎት ሄደ ። ይህን ሲያወሩ ፍየል ሰምታ ኖሮ ለፈረሱ ያወረቱን ሁሉ እያዘነች ነገረችው ። በ3ተኛው ቀን ሀኪሙ መጣ ፈረሱም ለውጥ አላሳየም ይህን ጊዜ ሊገሉት ወሰኑ ጓደኛዬ አንተን ማጣት አልፈልግም ። ሳይገሉህ በፊት ሸክም አለመሆንህን ተነስተህ አሳያቸው ብላ እያለቀሰች ለመነችው በፍየሏ ግፊት እንደ ምንም ተነስቶ መሮጥ ጀመረ ። ገበሬው እና ሀኪሙ ያዩትን ማመን ገበሬ በፈረሱ መዳን ተደስቶ ፍየሏን አርዶ በላት ። ይህ የአለም መራር እውነት ነው ። መልካም ስራ ሰርታችሁ በምስጋና ፈንታ ውርደትን ትሸለማላችሁ ። ያም ቢሆን ግን ቅን ሰው ከመሆን አትቦዝኑ 2.2K views , edited 09:20