አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የ24ስዓት የተጋድሎ ውሎ
ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም
_______፩
አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ከሌሊቱ 11:30 ጀምሮ ከምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ በ27ኪ.ሜ ርቀት ከምትገኘው ረቡዕ ገብያ ከተማ በመነሳት ወደ ዳንጉሌ ቀበሌ እንቀሳቀሳለሁ ባለ ጠላት ላይ ባደረገው ትንቅንቅ የሜጀር ጀነራል ብርሀኑ ጥላሁን ሰራዊት አመድ በማልበስ
1 ሞርተር
1 ዲሽቃ
4 ብሬን
ስናይፐርን ጨምሮ ለቁጥር የሚከብድ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ማርኳል።
ለስድስት ቀናት ተንኳቶ ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ጮቄ ተራራ ለመውጣት በተንቀሳቀሰው የአረመኔው ሰራዊት ላይ የተቀናጀ ውጊያ የከፈተው 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ጠላትን በመረፍረፍ ታሪክ ሰርቷል።
የ206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር አሃዶች በዕሮቡ ገበያ በመግባት የጠላትን ኃይል በማዛባት ግዳጇን በብቃት ተወጣለች።
በተመሳሳይ በዚ አውጊያ 109ኛ ኮር 99ኛ ክፍለጦር ሽፋን በመስጠት ሲያግዝ ቆይቶ ቆረጣ በመግባት 1ዲሽቃ መማረክ ችሏል።
ከፍትኛ ቁርጠኝነትና ጀግንነት በታየበት በዚህ ውጊያም ከአንድ ሻለቃ በላይ የአረሠኔው ሰራዊትን መደምሰስ ተችሏል።
_______፪
ከተማ ውስጥ መሽገው ሕዝብ ሲሚያሰቃዩ የነበሩ አመራሮችን በመምታት መሳሪያቸውን በመያዝ ፋኖን ተቀላቀሉ።
ወጣት ዘላለም በለጠ ይባላል። ተወልዶ ያደገው ሰከላ ወረዳ አቻይታ ቀበሌ ሲሆን። የሚኖረው አዲስ አበባ ነበረ። ነገር ግን ጠላት አጉት የሚኖረውን የአጎቱን ልጅ ምላሱንና ብልቱን መቁረጡን ሲሰማ ከአዲስ አበባ ወደ ሰከላ ወረዳ ግሽ አባይ ከተማ በመመለስ ሻለቃ መሪውን በጩቤ ወግቶ ክላሹንና ሽጉጡን በመማረክ የአጎቱን ልጅ ገዳይ በመበቀል 44ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅሏል።
በተመሳሳይ ይልማና ዴንሳ ወረዳ አዴት ከተማ ላይ ሻንበል በለጠ የተባለን የሚሊሻ ሀላፊ መሳሪያ እሳት የላሰው ጀግና ወጣት መሀል ከተማ ላይ በዱላ ማጅራቱን ብሎ ሰደፍ ክላሽ ማርኮ 102ኛ ኮር 11ኛ ክፍለጦር አንሙት ያዛቸው ሻለቃን ተቀላቅሏል።
ግፍ ሕዝብን የበለጠ እንዲታገል በማድረግ ትግልን የበለጠ ያፋጥናል ። ስለሆነም ግፍን ተፀይፈው ፋኖን የተቀላቀሉ ወንድሞችን እንኳን ደና መጣችሁ እንላለን።
አዲስ ትውልድ፣አዲስአስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብኃ| ቴወድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም