የተማሪዎች መግቢያ ጥሪ ማስታወቂያ በ2014 የትምህርት ዘመን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ግንቦት 1 እና 2 ሲሆን ምዝገባ የሚካሄደው ግንቦት 3 እና 4 እንዲሁም ትምህርት የሚጀመረው ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓ.ም ይሆናል፡፡ በመሆኑም ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡- የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ኦርጂናልና ኮፒ፣ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል የተማራችሁበት ትራንስክሪፕት ኦርጂናልና ኮፒ፣ የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ኦርጂናልና ኮፒ፣ አራት ፓስፖርት ሳይዝ የሆነ ጉርድ ፎቶ፣ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ፣ እንዲሁም ኮቪድ-19ን ለመከላከል የሚያስችል የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል (ማስክ) በመያዝ ሳውላ ካምፓስ የተመደባችሁ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፣ በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኙ ካምፓሶች የተመደባችሁ በየካምፓሶቻችሁ በሚገኙ የሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የተመደባችሁበት ካምፓስ መረጃ ከዩኒቨርሰቲው ድረ-ገጽ www.amu.edu.et ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንዲሁም ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት 7.8K views06:56