2023-05-06 20:20:31
አንቺ ከሔድሽ ወድያ
------- ----------- ---------
በሔድንበት መንገድ
ባለፍኩኝ ቁጥር፤
ድቅን ይልብኛል
እንዲያው ያንቺው ፍቅር።
የፍቅር ፈላስፋው
ጠፍቶት ፍልስፍናው፤
ፍቅርን ለመግለጥ
እንዳንቺ ሲያቅተው፤
ቃላቶች የሉኝም
ሲል ሰማነው።
ያኔ.... ከሔድንበት...
ካትክልቱ ስፍራ፤
እንዲያ ብለሽ ነበር ፍቅርን ስናወራ።
"ስንት እጅ አለክ?" እሷ
"ሁለት" እኔ
"ስንት እግር፣ዓይን፣ጆሮ.....አለክ?" እሷ
"ሁለት" እኔ
"አየህ ሁለነገራችን ሁለት ሀለት ነው አደል?" እሷ
"አው ሁለት ሁለት ነው !" እኔ
"እእ ስንት ልብ አለክ?" እሷ
" እእእ አንድ" እኔ
" አየኽ ፍቅር ማለት ያቺ አንድ የሆነችውን ልብ ፈልጎ ማግኘት ነው።" እሷ
"አው ቀትክክል" እኔ
"እና ፍቅር ማለት የጎደለውን ልብ መሙላት ነው። አፈቅርሀለው" እሷ...
ታድያ ይህ ፍልስፍና፤
ባያረግሽ እንኳ ታዋቂ ገናና፤
በቶሎ ተመለሽ በልቤ ነግሰሻልና።
አንቺ ከሔድሽ ወድያ አካላቴ ዝሎ፤
ከመንገድ ምባዝን ሆንኩ እንደበቅሎ።
ከቃልሽ መሀከል ይሕ ትዝ እያለኝ፤
በሔድንበት መንገድ መጓዙን ቀጠልኩኝ።
ፍቅርሽን እያሰብኩ ትካዜ ወረረኝ፤
አንቺን ከሔድሽ ወድያ እንዲ ነው ሚረገኝ።
ምንተስኖት ሱሌይማን
ቀን፦11/09/2014
@getami_mintesnot
52 views17:20