የባልደራስ ም/ፕሬዝደንት አቶ አምሀ ዳኜው በፀጥታ ኃይሎች ታፈኑ።
አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ
መጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ሸዋ
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት አምሀ ዳኜው መጋቢት 23/2015 ዓ.ም ምሽቱን በደህንነት ኃይሎች እና በፌደራል ፖሊስ ታፍነው ተወስደዋል።
አቶ አምሀ ዳኜው ታፍነው የተወስውዱት ከመኖሪያ ቤታቸው ነው።
ከዚህ ቀደም በመጋቢት 2/2015 ዓ.ም በኦህዴድ/ብልፅግና መንግስት የታጠቁ ኃይሎች ለሰዕታት ታግተው እንደነበር ይታወሳል ሲል ባልደራስ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።