ሀሰን ሼክ መሃመድ 10ኛው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ
ለሁለት ዓመታት የተራዘመው የሶማሊያ ምርጫ በዛሬው እለት ተካሂዷል።
በምርጫውም ሀሰን ሼክ መሃመድ አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት በመሆን ተመርጠዋል።
ሀሰን ሼክ መሃመድ የሶማሊያ ፓርላማ በ3 ዙር ባደረገው ምርጫ በስልጣን ላይ ያሉትን መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆን በመርታት ነው 10ኛው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት በመሆን የተመረጡት።
ተመራጩ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ ከዚህ ከቀም በፈረንጆቹ ከ2012 እስከ 2017 ሶማሊያን በፕሬዝዳንትነት መርተው እንደነበረ ይተወዋል።
t.me/AlGhaziMedia