2022-08-20 08:33:10
እጅግ በጣም ሩኅሩኅና አዛኝ በሆነዉ በአላህ ስም
እስልምና ወደ ሃገራችን ከሌሎች አለም ቀደም ብሎ እንደውም ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም ሂጅራ ከማረጋቸውም በፊት ከገባበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በጠንካራ እና ጽኑ
ኡለማዎች ቅብብል መስዋትነት ሲተላለፍ ቆይቷል
ባለፉት ጊዜያት በተደረጉ ጥናቶች ደሞ በኡለማ ቅብብሎሽ እኛ ጋር የደረሰው እስልምና
በሃገራችን በሶስት ዲናዊ መንፈሳዊ ስራዎች መስፋፋቱን ጥናቶች አረጋግጠዋል
እነዚህም ሀድራ መንዙማ እና መውሊድ ናቸው ።
ከነዚህ ሶስት እስልምናን ካስፋፉ የመሻሂኮቻችን የሂዳያ የ ዳእዋ መሳሪያዎች ውስጥ መውሊድ
ሁለቱን አቅፎ እንደመያዙ እና ለበርካቶች የሂዳያ የተውባ ሰበብ እንደመሆኑ መጠን ይህኛውም
ትውልድ የአባቶቹን ዲን ለማስቀጠል ብሎም መውሊድ ትላንት በሃገራችን ያስገኘውን መንፈሳዊ
እስላማዊ ስኬት እንዲያስቀጥል ነጃሺ እስላማዊ ማህበር ከተመሰረተ ጀምሮ የተለያዩ ስራዎችን
ሲሰራ ቀይቷል በዘንድሮም የ 1497ኛው መውሊድ
መሻኢኾቹ ተርቲብ ባደረጉት መሠረት ረሱላችን ሰዐወ(ምን) ረቢዑ እስኪቃረብ የተለያዩ
ዝግጅቶችን በማድረግ እንዲዘከሩ በየግዜው እንዲወሱ ማህበረሰባችን የበለጠ ስለ ነብያችን
ታላቅነት ይረዳ ዘንድ ቅድመ መዉሊድ የአራት እሁዶች የሚሸፍን መርሀግብር አዉጥተን
እየተንቀሳቀስን እንገኛለን
በዘንድሮው አመት ካወጣነዉ የመዉሊድ መርሀግብራችን የሚጀምረዉ ከላይ በገለፅነዉ መሠረት ከቅድመ መዉሊድ የማስተዋወቅ መርሀግብር ሲሆን
መርሀግብራችን እንደሚከተለዉ ይቀርባል
1 የመጀመሪያው መርሀግብራችን የምንጀምረዉ በየሆስፒታሉ ለሚገኙ ደም ለሚፈልጉ ታማሚ
ወገኖቻችን ደም የምንሰጥበት ይሆናል ይኸዉም የፊታችን የመጀመሪያው እሁድ 15/12/2014
ፒያሳ በሚገኝው በኑር (በኒ) መስጂድ ፓርኪንግ ግቢ ውስጥ "ደሜን ለወገኔ እሰጣለሁ
የአለማቱን ነብይ ውልደት አበስራለሁ" በሚል መሪ ቃል ደም በመለገስ ነብያችን ሰለላሁ
አለይሂ ወሰለም ያስተማሩንን ሰብአዊነትና የደግነት በተግባር በማሣየት ዉዴታችን ደስታችን
በመግለፅ የሚጀመር ይሆናል !!
2 ሁለተኛ ሳምንት እሁድ ሀገራችን ላይ ያሉ ታላላቅ ዑለሞች እና ለዚህ ዲን ባለውለታ የሆኑ
አካላትን በያሉበት አካባቢ በመገኘት የዚያራ እና የምስጋና ፕሮግራም በማድረግ የዲኑ መሪዎች
ዑለማዎች በመሆናቸው ከጎናቸው በመሆን ለነብዩ ያለን ደስታ ፍቅር እንገልፃለን !!
3 ሶስተኛ ሳምንት እሁድ የተቸገሩ ጧሪ ቀባሪ የሌላቸውን አረጋዊንን አንድ ማዕከል ላይ
በመገኝት የማቴሪያል እና አስፈላጊ ነገሮችን ድጋፍ በማድረግ ከአረጋውያኑ ጋር የመውሊድ
ኮንፍረንስ በማድረግ እየተደሰትን እናሳልፋለን!!
4 አራተኛ ሳምንት እሁድ መውሊድ ለምን እንደሚከበር እና ለዚህ ሙስሊም ዑማ ፋይዳው
ምንድን ነው? በሚል በዘርፉ አንቱ የተባሉ ዓሊሞች እና ምሁራን ኮንፍረንስ እና አውደርእይ ይካሄዳል !!
እነዚህ የዘረዘርናቸው ቅድመ መዉሊድ መርሀግብሮች እንዳጠናቀቅን የመጨረሻ መደምደሚያ
የሚሆነዉ ሁሌ በየአመቱ እንደምናደርገዉ ታላቅ የመዉሊድ ፕሮግራግራም ሁሉ በዘንድሮም
መውሊድ ከ10.000 (አስር ሺ) በላይ የነብዩ (ሰዓወ) ሙሂቦች የሚሳተፉበት በነብዩ ፍቅር እና
በዑለሞቻችን መንገድ ህያው ነን በሚል መሪ ቃል ታላቅ ሀገር አቀፍ መውሊድ ለሶስተኛ ጊዜ
አክብረን በዱዓ የምንዘጋ ይሆናል !!
አላህ የነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም መዉደድ መንገዳቸዉ መንገዳችን አድርጎ መያዝን
ይወፍቀን ከአላህ ምንዳ እና ፍቅር የምናገኝበት ያድርግልን አሚን !!
"በነብዩ (ሰዓወ) ፍቅርና በዑለሞቻችን መንገድ ህያው ነን"
ሙሉ ዜናውን በሀሪማ እና በአል ሱና ቲቪ ይከታተሉ!
147 views05:33