Get Mystery Box with random crypto!

@l islam Tube (ዊላዳውን አብሳሪ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ alislamtube — @l islam Tube (ዊላዳውን አብሳሪ) L
የቴሌግራም ቻናል አርማ alislamtube — @l islam Tube (ዊላዳውን አብሳሪ)
የሰርጥ አድራሻ: @alislamtube
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 986
የሰርጥ መግለጫ

ሼር ሼር @Al-islam-Tube (ዊላዳውን አብሳሪ)ሀቅን ለሚሹ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-26 21:51:54 አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ
~~~

ሱመያዊያን የበጎ አድራጎት ማህበር ለመቋቋም ከታቀደ ጥቂት ወራት አልፈውታል። ሀሳቡ በብዙ ሰው ዘንድ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ማህበሩን የመሰረቱት አባል ሸይኽ ሰዒድ ሁሰይን የሱመያ መስጂድ ኢማም እና ኸጢብ ማረፋቸውን ተከትሎ እያንዳንዱ የሚሰራው የኸይር ስራ አጅር ለእርሳቸው ይደርስ ዘንድ በማለት ቀድመው ጀምረውታል።

ማህበሩ የሚያተኮሩ በመሻይኾች ላይ ነው። የዑለሞቻችንን ወርቃማ የቀደመ ወደ ነብዩ ሙሐመድ የተሰላሰለ ሰነድ እስከ ቂያማ ድረስ ከትውልድ ትውልድ እንዲተላለፍ በማድረግ ዒልሞቻቸውን ፣ አውራዶቻቸውን ፣ ኪታቦቻቸውን እና ታሪኮቻቸውን ለማጥናት ብሎም በሀያት እያሉ ነዳማ ሳይመጣብን በፊት በሙሉ አቅም ለማገዝ እና ከጎናቸው ለመቆም የታቀደ አላማ ነድፎ ተነስቷል።

በአሁኑ ወቅት በጥቂት የመሻይኾች አፍቃሪ እና ወዳጅ በሆኑ ወጣት አባላት የተዋቀረ ሲሆን ስራው በስፋት ተደራሽ እንዲሆን እና ብዙ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርቶ ሙስሊሙን ማህበረሰብ በሀይማኖቱ እና በመሻይኾቹ ዙሪያ የነቃ ግንዛቤ እንዲኖረው ለማድረግ ይቻል ዘንድ ከፍተኛ ቁጥር ያለው አባል ያስፈልገዋል። ለዚህም ውድ ወንድም እና እህቶቻችን የመሻይኾችን መንገድ ለማስጠበቅ እና ለማስቀጠል ፣ መሻይኾቻችንን በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መንገድ እየደገፍን እና ታሪኮቻቸውን ለህዝብ እያስተዋወቅን ቀጣዩን ትውልድ ከአሁኑ እንቅረፅ።

ማንኛውም መሻይኾቼን እወዳለሁ ፣ ኢልማቸውን ማወቅ እፈልጋለሁ ፣ አውራድ እና ጦሪቃቸውን አስጠብቃለሁ የሚል ሰው የማህበሩ አባል መሆን ይችላል። ለአባልነቱ የተዘጋጀውን ፎርም በውስጥ መስመር

Telegram
ፈይሰል አብዱ(@Sumaliyano)
አብዱልሀኪም ናስር(@Hakiku01)
ኻሊድ አዳነ(@MERUEM222)
Facebook
ፈይሰል አብዱ
ጅብሪል አባስ (ibnu abas)
ኻሊድ አዳነ (azzrael azel)

በማነጋገር መሙላት ትችላላቹህ። ዝርዝር መረጃ ካስገለገ በስልክ ቁጥር

09 56 15 58 06 ኻሊድ አዳነ
09 11 26 55 62 ፈይሰል አብዱ
09 34 44 80 08 ራህመት ረዲ
በtelegeram channel
https://t.me/sumeya_charity_1
በ facebook ፔጅ ያግኙን

በመሻይኾች መንገድ ህያው!
የሱመያዊያን በጎ አድራጎት ማህበር
66 views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:10:31
የኑር መስጂድ ወጣት ጀመዐ

የታላቁ ነብያችን ﷺ ውልደት መቃረብን አስመልክቶ በመስጂዳችን በየ አመቱ የሚደረገው የታላቁ የረቢዕ ወር አቀባበል የዚክር ፕሮግራም የፊታችን ጁመዐ ከሰላት ቡሀላ በርካታ ወጣት ማዲሆች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ይጀመራል ።
742 views04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 20:56:48
ደሜን ለወገኔ እሰጣለሁ የነብዩን(ሰዓወ) ውልደት አበስራለሁ በሚል መሪ ቃል ለሶስተኛ ጊዜ የደም ልገሳ ፕሮግራም ይካሄዳል

ቦታ ኑር( በኒ ) መስጂድ ፓርኪንግ ግቢ
ቀን ነገ እሁድ ነሀሴ 15/2014
ሰዓት ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ

እንዳይቀሩ ደሞን ለወገንዎ ይለግሱ
በዊላዳው ተደሰቱ
133 views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 19:43:05
105 views16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 08:33:30
170 views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 08:33:10 እጅግ በጣም ሩኅሩኅና አዛኝ በሆነዉ በአላህ ስም

እስልምና ወደ ሃገራችን ከሌሎች አለም ቀደም ብሎ እንደውም ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ
ወሰለም ሂጅራ ከማረጋቸውም በፊት ከገባበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በጠንካራ እና ጽኑ
ኡለማዎች ቅብብል መስዋትነት ሲተላለፍ ቆይቷል
ባለፉት ጊዜያት በተደረጉ ጥናቶች ደሞ በኡለማ ቅብብሎሽ እኛ ጋር የደረሰው እስልምና
በሃገራችን በሶስት ዲናዊ መንፈሳዊ ስራዎች መስፋፋቱን ጥናቶች አረጋግጠዋል

እነዚህም ሀድራ መንዙማ እና መውሊድ ናቸው ።
ከነዚህ ሶስት እስልምናን ካስፋፉ የመሻሂኮቻችን የሂዳያ የ ዳእዋ መሳሪያዎች ውስጥ መውሊድ
ሁለቱን አቅፎ እንደመያዙ እና ለበርካቶች የሂዳያ የተውባ ሰበብ እንደመሆኑ መጠን ይህኛውም
ትውልድ የአባቶቹን ዲን ለማስቀጠል ብሎም መውሊድ ትላንት በሃገራችን ያስገኘውን መንፈሳዊ
እስላማዊ ስኬት እንዲያስቀጥል ነጃሺ እስላማዊ ማህበር ከተመሰረተ ጀምሮ የተለያዩ ስራዎችን
ሲሰራ ቀይቷል በዘንድሮም የ 1497ኛው መውሊድ
መሻኢኾቹ ተርቲብ ባደረጉት መሠረት ረሱላችን ሰዐወ(ምን) ረቢዑ እስኪቃረብ የተለያዩ
ዝግጅቶችን በማድረግ እንዲዘከሩ በየግዜው እንዲወሱ ማህበረሰባችን የበለጠ ስለ ነብያችን
ታላቅነት ይረዳ ዘንድ ቅድመ መዉሊድ የአራት እሁዶች የሚሸፍን መርሀግብር አዉጥተን
እየተንቀሳቀስን እንገኛለን

በዘንድሮው አመት ካወጣነዉ የመዉሊድ መርሀግብራችን የሚጀምረዉ ከላይ በገለፅነዉ መሠረት ከቅድመ መዉሊድ የማስተዋወቅ መርሀግብር ሲሆን

መርሀግብራችን እንደሚከተለዉ ይቀርባል

1 የመጀመሪያው መርሀግብራችን የምንጀምረዉ በየሆስፒታሉ ለሚገኙ ደም ለሚፈልጉ ታማሚ
ወገኖቻችን ደም የምንሰጥበት ይሆናል ይኸዉም የፊታችን የመጀመሪያው እሁድ 15/12/2014
ፒያሳ በሚገኝው በኑር (በኒ) መስጂድ ፓርኪንግ ግቢ ውስጥ "ደሜን ለወገኔ እሰጣለሁ
የአለማቱን ነብይ ውልደት አበስራለሁ" በሚል መሪ ቃል ደም በመለገስ ነብያችን ሰለላሁ
አለይሂ ወሰለም ያስተማሩንን ሰብአዊነትና የደግነት በተግባር በማሣየት ዉዴታችን ደስታችን
በመግለፅ የሚጀመር ይሆናል !!

2 ሁለተኛ ሳምንት እሁድ ሀገራችን ላይ ያሉ ታላላቅ ዑለሞች እና ለዚህ ዲን ባለውለታ የሆኑ
አካላትን በያሉበት አካባቢ በመገኘት የዚያራ እና የምስጋና ፕሮግራም በማድረግ የዲኑ መሪዎች
ዑለማዎች በመሆናቸው ከጎናቸው በመሆን ለነብዩ ያለን ደስታ ፍቅር እንገልፃለን !!

3 ሶስተኛ ሳምንት እሁድ የተቸገሩ ጧሪ ቀባሪ የሌላቸውን አረጋዊንን አንድ ማዕከል ላይ
በመገኝት የማቴሪያል እና አስፈላጊ ነገሮችን ድጋፍ በማድረግ ከአረጋውያኑ ጋር የመውሊድ
ኮንፍረንስ በማድረግ እየተደሰትን እናሳልፋለን!!

4 አራተኛ ሳምንት እሁድ መውሊድ ለምን እንደሚከበር እና ለዚህ ሙስሊም ዑማ ፋይዳው
ምንድን ነው? በሚል በዘርፉ አንቱ የተባሉ ዓሊሞች እና ምሁራን ኮንፍረንስ እና አውደርእይ ይካሄዳል !!

እነዚህ የዘረዘርናቸው ቅድመ መዉሊድ መርሀግብሮች እንዳጠናቀቅን የመጨረሻ መደምደሚያ
የሚሆነዉ ሁሌ በየአመቱ እንደምናደርገዉ ታላቅ የመዉሊድ ፕሮግራግራም ሁሉ በዘንድሮም
መውሊድ ከ10.000 (አስር ሺ) በላይ የነብዩ (ሰዓወ) ሙሂቦች የሚሳተፉበት በነብዩ ፍቅር እና
በዑለሞቻችን መንገድ ህያው ነን በሚል መሪ ቃል ታላቅ ሀገር አቀፍ መውሊድ ለሶስተኛ ጊዜ
አክብረን በዱዓ የምንዘጋ ይሆናል !!

አላህ የነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም መዉደድ መንገዳቸዉ መንገዳችን አድርጎ መያዝን
ይወፍቀን ከአላህ ምንዳ እና ፍቅር የምናገኝበት ያድርግልን አሚን !!

"በነብዩ (ሰዓወ) ፍቅርና በዑለሞቻችን መንገድ ህያው ነን"

ሙሉ ዜናውን በሀሪማ እና በአል ሱና ቲቪ ይከታተሉ!
147 views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 07:34:34
#መጅኑኑ_ለይላ
*******
መጅኑኑ ለይላ መፅሀፍ እነሆ በቅርቡ የህትመት ጣጣውን ጨርሶ ወደናንተ ይደርሳል። በመፀሀፉ ላይ ቀድመን የለቀቅነው የሽፋን ምስልም ለውጥ ተደርጎለታል። የመፅሀፉን የምርቃት ፕሮግራም በድምቀት የምናከብርበትንና በይፋ ለገበያ የሚበቃበትን ቀንም በቅርብ የምናሳውቅ ይሆናል።

ደራሲው ሷሊህ አስታጥቄ እና የአል ፋሩቅ መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን ባለቤት ፋሩቅ ጋሊብ
101 views04:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 22:27:54
ምርጥ ደአዎ
100 views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 07:32:31
የፊታችን እሁድ ነሐሴ 15/2014 በታላቁ ኑር መስጂድ የደም ልገሳ ፕሮግራም አለ ደምዎን ለወገንዎ ይለግሱ። ለደም ልገሳ ሲመጡ ለአረጋውያን የሚሆን አልባሳትን ይዘው እንዲመጡ ይበረታታል። እለቱን በደም እጥረት ህይወታቸውን ለሚያጡ እና ጧሪ ቀባሪ ለሌላቸው አዛውንት አልባሳት የምናሰባስብበት ይሆናል።

የፕሮግራሙ ዓላማ አሽረፈል ኸልቅ ረሱል ሶለላሁ ዓለይ ወሰለም ለዓለም እዝነት መላካቸውን በተግባር ለመግለፅ በመሆኑ አቅም ለሌላቸው እዝነትዎን ያሳዩ ዘንድ ተጋብዘዋል!
1.3K views04:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 21:11:24
የሼህ ኡስታዝ ፈድሉ ዱአ
128 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ