2022-06-30 10:41:06
ሰላም እንዴት ናችሁልን ውድ የአለውያ ቤተሰቦች
ቀደም ሲል ፖስት የተደረገው መልእክት የተዛባ ትርጓሜ የሚሰጥ መሆኑን ከናንተው ውድ ደንበኞቻችን በተሰጠ አስተያየት ተገንዝበናል።
በመጀመሪያ ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ እየጠየቅን መልእክቱን እንደሚከተለው እናብራራለን።
እንደሚታወቀው የምንሰጠው የፀጉር እንክብካቤ ያለማቋረጥና ያለመሰልቸት መወሰድ ያለበት ነው። በዚያ መንገድ ትሪትመንቱን የተከታተላቹ ደንበኞች ከፍተኛ ለውጥ መታዘባችሁን አጋርታችሁናል።
ይሁንና አንዳንድ ደንበኞች ምንም እንኳን የወር ፓኬጅ ቢከፍሉም በየሳምንቱ ቀናቸውን ሳያዛንፉ መምጣት ሲኖርባቸው በየመሀሉ ሳይመጡ እየቀሩ ክፍተት ይፈጠርና የተፈለገው ለውጥ ሳይመጣ ይቀራል።
ይህን ለመታደግ አዲስ አሰራር ዘርግተናል።
ማንኛውም ደንበኛ የወር ከከፈለ በኋላ ቀኑን ሳይጠብቅ በመቅረቱ ምክንያት 4 ጊዜ ሳይጠቀም ቀርቶ ወሩ ቢያልቅ ፓኬጁ ኤክስፓየር ያደርጋል ማለት ነው። የግድ በየሳምንቱ አንዴ በወር አራት ጊዜ መጠቀም ይኖርባችኋል።
ልክ ከቴሌ የወር የኢንተርኔት ፓኬጅ ገዝታችሁ ሙሉውን ተጠቀማችሁትም አልተጠቀማችሁትም ወሩን ጠብቆ እንደሚቋረጠው ማለት ነው።
ያ ማለት ግን ከዚያ በኋላ ሌላ ፓኬጅ ገዝታችሁ አገልግሎቱን ደግማችሁ መጠቀም አትችሉም ማለት አይደለም።
ይህን ለማድረግ ያነሳሳን-
1ኛ) በዋናነት ከአገልግሎቱ ማግኘት ያለባችሁን ለውጥ እንዳታገኙ እንቅፋት በመሆኑ እና
2ኛ) ጊዜያቸውን ጠብቀው ሳያዛንፉ የሚጠቀሙ ሌሎች ደንበኞቻችንን ለማስተናገድ ያልተገመተ ወረፋ ስለሚፈጠር ደንበኛ እያስከፋን በመሆኑ ነው።
እናመሰግናለን።
1.6K viewsedited 07:41