Get Mystery Box with random crypto!

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በነበረው የጸጥታ ችግር ተፈናቅለው በተለያ | አድማስ ሬድዮ- Admas Radio

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በነበረው የጸጥታ ችግር ተፈናቅለው በተለያዩ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ያሉትን ዜጎች መልሶ ለማቋቋምና ለመደገፍ  የሚያስችል ከ14 ሚሊዩን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን  በክልሉ የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመደገፍ  የተቋቋመው የገቢ አሰባሰብ አብይ ኮሚቴ አስታውቋል።

የቤኒንሻጉል ጉሙዝ ክልል የግብርና እና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ እንዳስታወቀው ገቢው የተሰበሰበው በክልል ደረጃ ካሉት ተቋማት እንዲሁም ከዞንና ወረዳ  ደረጃ ካሉት መስሪያ ቤቶች ነው።ከዚህ ቀድም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለክልሉ ተፈናቃዩች የተላከው ድጋፍ  በአሶሳ ዞን ሆሞሻ በተባለ  ወረዳ ተራግፎ የነበረና በቶሎ ተፈናቃዩች  አልደረሰም የሚል ቅሬታም ሲቀርብ የቆየ ሲሆን ከትናንት ጅምሮ ወደ ስፋራ ማጓጓዝ መጀመሩንም ገልጿል።

(ዶቼቬሌ DW)
@admasradio