✞እያለፈ ነው ዘመኔ✞ እያለፈ ነው ዘመኔ ትእዛዙን ሳልፈጽም ወየው ለእኔ(፪) በጠራኝ ጊዜ ምን እላለሁ ና ብሎ ወደእኔ(፪) በወጣትነቴ ሳልሠራ እያየሁ አለፈኝ ብዙ አዝመራ(፪) ከእንግዲህ በመሥራት ጌታ ሆይ ልኑር ከአንተ ጋራ(፪) የማስብበት በየለእቱ ንጹሕ ልብን ስጠኝ አቤቱ(፪) ከትእዛዝህ ውጪ በመሆን እዳልቀር በከንቱ(፪) እንደየሥራው ለመስጠት በግርማ መንግሥቱ ሲመጣ(፪) ማን ይሆን የሚቆም ከፊቱ ፊተናን የወጣ(፪) እንዳያስቷችሁ ተጠንቀቁ እየተማራችሁ ከቃሉ(፪) ይመጣሉና በእርሱ ስም አምላክ ነን የሚሉ(፪) ትእግሥትን በመያዝ ሁላችሁ እስከመጨረሻው ጠንክሩ(፪) ያን ጊዜ ይሆናል በእርሱ ዘንድ የማዳን ተግባሩ(፪) "በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ" መክ፲፪፥፩ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ mazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ 333 viewsedited 05:46