#አማኑኤል_ተመስገን አማን በአማን(፬) አማኑኤል ተመስገን ለዚህ ፍቅርህ ምን ልክፈልህ (፪) ድብቁን ኃጢአት አንተ ብትገልጸው ይቅር ብለኸኝ ባትሸፋፍነው እንደ ሰው በቀል ቢኖር ጌታ ለኔ ኃጢአትስ የለውም ቦታ #አዝ በየደቂቃው ኃጢአት ስሰራ ስሰርቅ ስበድል አንተን ሳልፈራ አንተ ግን ፊትህ ምንም ቢቀየም በቁጣህ በትር አልገረፍከኝም #አዝ ምህረትህን ልከህ አድነኝ ዛሬ ታክቶኛልና በኃጢአት መኖሬ አለም በኃጢአት እየሳበችኝ በጽድቅ ደስታ መኖር አቃተኝ #አዝ የኃጢአት ጉዞ ጣፋጭ ቢመስልም ውጤቱ መሮ ፍጹም አይጥምም እንደ በደሌ ስላልከፈልከኝ ተመስገን እንጂ ሌላ ምን አለኝ ✥┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈✥ ✣ ✢ ✥┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈✥ 320 viewsedited 06:12