2022-06-06 14:07:56
የህገ ዝንየት መሠረት በኦርቶዶክስ
ዝንየት ማለት ባጭሩ ጸያፍ ህልም ማለት ሲሆን አንድ ወንድ ተኝቶ መጥፎ ህልም በማየትም ይሁን ባለማየት ሳያውቀው በእንቅልፉ የዘር ፈሳሹ ሲፈሰው ማለት ነው። ሙስሊሞች 'ኢህቲላም' የምንለው በእንግሊዝኛ wet dream የሚባለው ነው።
የዝንየት ህግ በኦርቶዶክስ ቅዱሳት መጽሐፍት ታሪካዊ አመጣጥና መሠረት እንዳለው በተአምረ ማርያም መጽሐፍ ተአምር ቁጥር 58 ላይ ተጽፎ ይገኛል (የተአምር ቁጥሩ በአንዳንድ የተአምረ ማርያም መጽሐፍት እትሞች ሊለያይ ይችላል ለምሳሌ 41ኛ ተአምር ላይ የምታገኙባቸው ሁኔታዎች አሉ)።
ታሪኩ ላይ በአንድ ንጉስ በወርቅ፣ በብርና በሀር የተጌጠች በውስጧ በጣም ብዙ ለታቦቱ ተብሎ ንጉሱ የሰጠው ገንዘብ የተቀመጠባት በማርያም ስም ተሰይማ የተሰራች ቤተክርስቲያን ነበረች(በመሠረቱ አንድን መንፈሳዊ የአምላክ ቤት በጣም ውድ በሆኑ ስጋዊ ጌጦችና ገንዘቦች ማስዋብ ይቻላልን? የሚለው ጥያቄ በውስጥ አዋቂነት ይያዝልኝ)። በቤተክርስትያኗ ውስጥ ያለው በጣም ብዙ ገንዘብ ከመሆኑም የተነሳ ንጉሱ የማያውቀውና በቤተክርስትያን ዙርያ ያሉ የክርስትያን ልጆች የማያውቁት አንድም ሰው ወደዚያች ቤተክርስቲያን አይገባም ነበር።
የሚያገለግሏት ካህናት ሁሌ ቀንና ማታ እየተፈራረቁ ይጠብቋትም ነበር ይላል ታሪኩ።
ቀጥሎም፥ አንድ ቀን በቤተክርስቲያን ቅጽር ውስጥ ሌሊቱን ሙሉ ሲጠብቁ ካደሩት ካህናት መካከል አንዱ ካህን ዝንየት(wet dream) መታውና የስጋው ዘር ፈሰሰው። ከዛ የማርያም ተአምር ሲገለጥ ሰውየውና በዙርያው ያሉ ወንድሞቹም ማናቸውም ሳያውቁ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ ዝንየት የያዘውን ሰው እንደተኛ ከቤተክርስቲያን ቅጽር 80 ክንድ ያህል አርቆ ወስዶ አሳደረው። ሰውዬውም አድሮ እስኪነቃ ድረስ የት እንዳደረና ዝንየት እንዳገኘው እንኳን አላወቀም ነበር ይላል ታሪኩ።
ይህ ክስተት ከተከሰተ በኋላ ከንጉስና ከጳጳስ ዘንድ አዋጅ ነጋሪ ወጥቶ ማንም ቄስ፣ ዲያቆን፣ መነኩሴም ይሁን ምዕመን #ህልመ #ዝንየት #ያገኘው #ሰው #ወደ #ቤተክርስቲያን #ቅጽር #ጊቢ #የገባ #ባባታችን #በሐዋርያት #ቃል #የተወገዘ #ይሁን ተብሎ አዋጅ ተነገረ።
በምስሉም በቀይ የተከበበው ቁጥር 21 ላይ እንደምትመለከቱት ከዚህ ገጠመኝ ቀን በኋላ ቢሆን እንጂ ከዚህ በፊት እስከዚች ክስተት ጊዜ ድረስ ይህ ህግና አስተምህሮ ማለትም ዝንየት እዳ መሆኑንና እስከዚህ ገጠመኝ ድረስ የዝንየት ህግና ስርአት ስለማይታወቅ ዝንየት አይቶ ቤተክርስቲያን ከመግባት የተቆጠበ ሰው ኖሮ እንደማያውቅ በጥቅሉ በኦርቶዶክስ ስርአት የዝንየት እዳና ህግ እንደማይታወቅ በግልጽ ይናገራል።
ዝርዝሩን ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ላይ ተአምር ቁጥር 58 ወይም 41 ላይ ይመልከቱ።
ጥያቄዎቻችን
1) ኢየሱስና ሐዋርያቱ ከኖሩበት 1ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ ይህ የዝንየት ህግና ስርአት ምንም ሳይታወቅና ዝንየት የመታው ክርስትያን በተአምረ ማርያም የተጠቀሰው መቸቱ(መቼና የት) እንዲሁም በማን እንደሆነ የማይታወቀው ክስተት እስኪከሰትና በቅዱሳት መጽሐፍት ጸድቆ ለመላው ኦርቶዶክሳዊ ስርአቱ እስኪታወቅ ድረስ ለብዙ ማለትም ለአስራ ምናምን ክ/ዘመናት በቤተክርስትያን የዝንየት ህግ ሳይታወቅ ቆይቶ ተአማኒነቱ ማለትም መቼ፣የትና በማን? የሚሉትን ጥያቄዎችን በማይመልስ አንድ የኋላ ክስተት እንዴት ህግ ተደርጎ ሊጸድቅ ይችላል? ታሪኩ ላይ የባለ ታሪኩን ጨምሮ የማንም ስም እና ክስተቱ የተፈጸመበትን ጊዜ የሚገልጽ ምንም አይነት ማስረጃ አለመኖሩ በራሱ የታሪኩን ታማኝነትና ትክክለኛነት ጥያቄ ውስጥ ሊከተው አይችልም?
2) የዝንየት ስርአትና ህግ በብሉይ ኪዳን መጽሐፍት በኦ. ዘሌዋውያን እና በኦ.ዘዳ በተለያዩ ጥቅሶች ዝንየት የነካው ሰው የተቀደሰን ነገር እንዳይነካና ወደተቀደሰ ነገር እንዳይቀርብ ለ1 ቀን ከሰፈር ሁሉ ርቆ እንዲቆይ በግልጽ [“ከመካከላችሁ ሌሊት ዘር በማፍሰስ የረከሰ ሰው ቢኖር ከሰፈር ወጥቶ እዚያው ይቈይ።”—ዘዳግም 23፥10] ተብሎ ተነግሮ ሳለ፥ በኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ይህ ህግና ስርአት ለብዙ መቶ ክ/ዘመናት አይታወቅም ነበር ስትል ቤተክርስትያኒቱ የብሉይ ህግጋትን ባለማንበቧና ባለማወቋ ነው ወይስ ይህ የብሉይ ህግ በወንጌል ተሽሯል ብላ ስላመነች ነው?
3) የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የብሉይ ኪዳኑ የዝንየት ህግና ስርአት ተሽሮ እንደነበር በማመኗ ከሆነ ለዘመናት ህጉን ያልፈጸመችው፥ ህገ ዝንየት በወንጌል ስለመሻሩ ቤተክርስትያን ማስረጃዋ ምንድነው?
4) ተሽሯል ቢባል ራሱ በኢየሱስና ሐዋርያቱ ወንጌል ለብዙ ዘመናት ተሽሮ የነበረን ህግና ስርአት ከዛ ሁሉ ጊዜ በኋላ መልሶ ህጉንና ስርአቱን የማጽደቅ ስልጣን ለአንድ ማንነቱና መቸቱ የማይታወቅ ካህንና ለገጠመኙ ሲባል እንዴት ሊሰጠው ይችላል?
5) በየትኛውም ዘመን ተአምር ተገለጠ፣ ገጠመኝ ታየ እየተባለ ለዛውም በግልጽ ማንነታቸው፣ መቼና የት እንደሆነ ባልታወቁ ግለሰቦች ምክንያት አዳዲስ ህግጋትና ስርአቶችን ወደ ቤተክርስቲያንና ክርስትና መጨመር በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ይቻላል?
https://t.me/Orthodox_Critic
185 views11:07