በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ ክስ ተመሰረተ የሳምንታዊው “ፍትሕ” መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር በሆነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 21፤ 2014 መደበኛ ክስ ተመሰረተ። ዐቃቤ ህግ በተመስገን ላይ የክስ መዝገብ የከፈተው፤ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የህግ መንግስት እና የሽብር ጉዳዮች ወንጀል ችሎት መሆኑን የጋዜጠኛው ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) 6.3K views15:00