Get Mystery Box with random crypto!

ውዳሴ ማርያም የሚጸልይና የማይጸልይ የእመቤታችን ውዳሴ ማርያም የዕለቱን | የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ትምህርቶች የሚተላለፉበት

ውዳሴ ማርያም የሚጸልይና የማይጸልይ

የእመቤታችን ውዳሴ ማርያም የዕለቱን ውዳሴ ማርያም በየዕለቱ የሚጸልይ ሰው የእናት አባቱን ርስት የወረሰ ይመስላል።

የሰባቱን ዕለት ውዳሴ ማርያም በእድሜዋ ልክ በየዕለቱ የሚጸልይ ደግሞ የዘመዶቹን ጨምሮ የወረሰ ይመስላል።

እመቤታችን ሳያመሰግን የሚውል ሰው ምን ይመስላል ቢሉ፦

ከሰው ቤት ድግስ ተጠርቶ ሂዶ በር ላይ ሲደርስ ውኃ ተደፍቶበት፥ ተቆጥቶ የሚመለስ፤ እንቅፋት እየመታው እየወደቀ እየተነሣ እየተሰበረ የሚሄድ ይመስላል።

ያ ሰው ካለመብላቱ በላይ እየተሰበረ እንደሄደ እመቤታችን የማያመሰግንም በመከራ ሥጋ ላይ መከራ ነፍስ ይጸናበታል። በርደተ መቃብር ላይ ርደተ ገሃነም ይጨመርበታል።
እኛ ግን፦
"አማንኬ ይደልወኬ አስተብፅዖ እስመ ኮንኪ እሞ ለእግዚአብሔር አዶናይ -የከሃሊ ኩሉ እግዚአብሔር እናት ሆነሻልና ብፅዕት መባል በእውነት ይገባሻል" እንላታለን።
ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ





ነገ ሐምሌ 15 የቅዱስ ኤፍሬም ዓመታዊ በዓል በመሆኑና የጸሎትን ክብር በመረዳት ውዳሴ ማርያምን የ7ቱን ዕለታት በመጸለይ ከድንግል ማርያም በረከትን እንቀበል።

የብሉያት እና የሐዲሳትን መጻሕፍት ከምንጩ ይማሩ።

https://t.me/AbaGebrekidangubaetezekro