2022-07-16 22:01:20
#ዓመቱ_ከማለቁ_በፊት_በጎ_ስራ_ስሩበት
በጎ አድራጎት ድርጅታችን ከሰኞ ሐምሌ 11 ጀምሮ በይፋ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ይጀምራል።ተማሪዎችን በልዩ ልዩ መልኩ መርዳት ከፈለጉ የምንፈልጋቸውን እንጠቁምዎ
አልባሳትና ጫማዎች እንፈልጋለን።አዳዲስ ገዝተው አሊያም ያልተበላሹ አልባሳትና ጫማዎች ካሉዎት በቀጥታ መጥተው ራስዎ መስጠት ይችላሉ
ለአንድ ቀን ወይም ከዛ በላይ ለሆነ ጊዜ ለተማሪዎች የምሳ ወጪ ቢሸፍኑልን (በቀን ከ10,000 እስከ 20,000 ይፈጃል ብለን ግምት ወስደናል)
ስዕል መለማመጃ መሳሪያዎች (ወረቀት፣ላጲስ፣እርሳስ፣ማርከር...)እንፈልጋለን
80 ደርዘን ደብተርና በትንሹ 500 እስኪሪብቶ እንፈልጋለን
10 የእግር ኳስ መጫወቻ ኳስ ቢገዙልን
ለህፃናት ቲአትር የሚያስፈልጉ የአልባሳት ወጪዎችን ብትሸፍኑልን
ተማሪዎቻችን ዝናብ እንዳይመታቸው የሚያመላልሳቸው ሁለት ሰርቪስ መኪና ቢደግፉን።ለአንድ መኪያ ኮንትራት ለሁለት ወር እስከ 15,000 ብር ገምተናል
ለህፃናቱ ውዝዋዜ ስልጠና መለማመጃ ሞንታርቦ ኪራይ ብትሸፍኑልን
#ግዴላችሁም_የምንመኛትን_ኢትዮጵያ_ለማየት_ህፃናት_ላይ_እንስራ
ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ ስልካችንን ተጠቀሙ #0902404444
ሁሉንም ከአንድ ሰው ማግኘት ባንችል እንኳ ተጠራቅሞ ይምላልናልና የባንክ ቁጥራችን እነሆ ብለናል #1000448386377
በአካል ሊያገኙን ከፈለጉ ካዲስኮ ተ/ኃይማኖት ህንፃ 4ኛ ወለል ላይ እንገኛለን።
#ባይተርፈንም_ያለንን_እናላፍላለን
@AaSsKkAaL12341234
1.3K viewsBelo, edited 19:01